በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ጆሃንስበርግ ላይ ሠልፍ ተደረገ


ጃከብ ዙማ - የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት /ፎቶ - ፋይል/
ጃከብ ዙማ - የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት /ፎቶ - ፋይል/

ፕሬዚዳንት ዙማ መጤ-ጠል ጥቃቱን አወገዙ፡፡

/ፎቶ - ፋይል/
/ፎቶ - ፋይል/

please wait

No media source currently available

0:00 0:12:32 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

በደቡብ አፍሪካይቱ ደርባን ከተማ ካለፈው ሣምንት ዓርብ ጀምሮ በውጭ ሀገር ዜጎች ላይ የደረሱ ጥቃቶችን በመቃወም በበርካታ ሺሆች የተቆጠሩ ደቡብ አፍሪካዊያንና ሌሎች ፍልሰተኞች ዛሬ፤ ሐሙስ - ሚያዝያ 8/2007 ዓ.ም ሰላማዊ ሠልፍ አካሂደዋል።

“አፍሪካ አንድ ናት፤ የጥላቻ ጥቃት ይቁም” የሚሉ መፈክሮችን ይዘው እያሰሙም ነበር ሠልፈኞቹ፡፡

አንድ ኢትዮጵያዊን ጨምሮ በትንሹ ለአምስት ሰዎች ህይወት መጥፋት እንዲሁም ለበርካቶች መቁሰልና ለንብረት መውደም ምክንያት የሆነውን ሁከት የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚደንት ጄከብ ዙማ ዛሬ አውግዘዋል።

ግጭቱን በመሥጋት በጆሃንስበርግ ከተማ አንዳንድ ሠፈሮች እንዲሁም ደርባን ውስጥ የሚገኙ የኢትዮጵያዊያንና የሌሎችም ሀገሮች ዜጎች የንግድ ተቋማት ዛሬ ተዘግተው ውለዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

XS
SM
MD
LG