በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የተባበሩት መንግስታት በኤርትራ ላይ የጣለውን ማዕቀብ ለአንድ ዓመት አራዘመ


የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታ ምክር ቤት
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታ ምክር ቤት

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታ ምክር ቤት በኤርትራ ላይ የቆየውን ማዕቀብ ለአንድ ዓመት እንዲራዘም ወስኗል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታ ምክር ቤት ከዚ በፊት በኤርትራ ላይ የቆየውን ማዕቀብ የሚያጠብቅ ውሳኔ መውሰዱ ይታወሳል። በትናንትናው ምሽት ማዕቀቡ ለአንድ ዓመት እንዲራዘም የጸጥታ ምክር ቤቱ መወሰኑ ታውቋል።

የውሳኔው መዝገብ ከዚህ በፊት በቀረቡት ክሶች ላይ ተመርኩዞ ሲሆን፣ ኤርትራ አል-ሸባብን ትደግፋለች፣ ከጅቡቲ ጋር ያልቋጨችው የድንበር ጉዳይ አለ፣ ማለትም በእአአ 2008 ያሰረቻቸውን ወታደሮች የመፍታት ክሶችን ያጠቃልላል።

የምክር ቤቱ ዋና ጸኅፊ እንግሊዛዊው አምጋሳደር ማትው ራይክፍርት (Mathew Rycroft) ውሳኔውን እንዲህ ሲሉ ገልጸዋል።

"የኤርትራና የሶማልያን ጉዳይ በተመለከተ ለየጸጥታ ምክር ቤቱ ፕረዚደንት እንደተገለጸው፣ ከዚህ በፊት ተጽፎ ለውሳኔ በቀረበው የሃሳብ ሰነድ S/2015/810 ድምጽ ለመስጠት የምትፈልጉ እጃቹን አንሱ። የድምጽ አሰጣጡ ውሳኔ ይህንን ይመስላል፣ 14ቱ በመደገፍ ድምጻቸውን ሲሰጡ፣ የተቃወመ የለም። 1 ድምጸ ተአቅቦ አድርጓል። ረቂቀ ሰነዱ 22/44 በመባል አልፏል" ብለው ገልጸዋል።

የኤርትራ መንግስት በበኩሉ ውሳኔውን ህግ የጣሰነ ነው በማለት አጣጥሎታል። ዛሬ የደረሰንን አጭር ዘገባ የድምጽ ፋይሉን በመጫን ይዳምጡ።

የተባበሩት መንግስታት በኤርትራ ላይ የጣለውን ማዕቀብ ለአንድ ዓመት አራዘመ /ርዝመት -1ደ23ሰ/
please wait

No media source currently available

0:00 0:01:22 0:00

ከዚህ በፊትም ኤርትራን ወክለው በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ሰባኛ ጉባኤ የተሳተፉትን አባሎች በፎቶ መድብላችን አቅርበን ነበር። ከዚህ በታች ያለውን ፋይል በመጫን ፎቶዎቹን ይመልከቱ።

XS
SM
MD
LG