Last updated at: 26.12.2012 00:28
<h1>“ስወድሽ” - ሚካኤል በላይነህና ገብረ ክርስቶስ ደስታ</h1><img src="http://amharic.voanews.com/App_Themes/VOA_am-ET/img/colorLogo.gif"/>ምርጥ ሥዕሎቹና የግጥም ሥራዎቹ ዘመን ተሻግረው ዛሬም የአያሌ ሚልዮን ኢትዮጵያውያን የኪነ-ጥበብ አድናቂዎችን ቀልብ እንደሳቡ ነው፤ ሠዓሊና ገጣሚ ገብረክርስቶስ ደስታ።<br /> <br /> የጥበብ አዋቂዎች በታላቅ አድናቆትና አክብሮት የሚያወሱት ይህ ሠው በህይወት ካለፈ ሦሥት አሥርታት ቢቆጠሩም፥ “ስወድሽ-ስወድሽ’ን” የመሳሰሉ ውብ ህያው ሥራዎቹ እንደ አዲስ ነፍስ ዘርተውና ገዝፈው በሌላ ግሩም ሥልት ተቀምመው በጆሯችን መንቆርቆር ከበቁ ምናልባትም ቀዳሚ እንጂ የመጨረሻ ከማይሆኑ ሥራዎቹ ውስጥ ናቸው።<br /> <br /> ድምጻዊ ሚካኤል በላይነህ በቅርቡ «ናፍቆት፤» በሚል ርዕስ ለአድማጭ ጆሮ ባበቃው አዲስ ሲዲው በተካተተችው “ስወድሽ” ዙሪያ እናወጋለን።<br /> <br /> ከሚካኤል በላይነህ ጋር ያደረግነውን ወግ ከዚህ ያድምጡ።<br /> <br /> <ul> <li class="listenlink"><a class="listenico" target="_blank" href="/audio/Audio/242872.html" onclick="opened=winOpened(); if (!opened) window.__playerWindow = window.open(winUrl(4,'242872',true),winName(),winSettings); winSetup(4,'242872',true, opened);return false;">“ስወድሽ” - ሚካኤል በላይነህና ገብረ ክርስቶስ ደስታ</a></li> </ul><link rel="canonical" href="http://amharic.voanews.com/content/michael-belayneh-gebre-kirstos-siwodish-12-23-12/1572119.html"/><meta name="syndication-source" content="http://amharic.voanews.com/content/michael-belayneh-gebre-kirstos-siwodish-12-23-12/1572119.html"/><img src="http://livetracker.voanews.eu/counter.lt?PageType=256&RecordId=1572119&SiteId=404&r=581030996&it=0&pd=20121225212822&url=ArticleID1572119" alt="" style="border:none;" height="1" width="1">
Copy to clipboard Close