በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ዜና ዕረፍት


ወይዘሮ ገነት ዘውዴ
ወይዘሮ ገነት ዘውዴ

ባልደረባችን ሰሎሞን ክፍሌ ባለቤቱን አጥቷል፡፡

ወይዘሮ ገነት ዘውዴ
ወይዘሮ ገነት ዘውዴ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:37 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

የሰሎሞን ክፍሌ ባለቤት ወ/ሮ ገነት ዘውዴ ያረፈችው በጠና ታምማ ላለፉት ሦስት ወራት ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ጆርጅ ዋሽንግተን ሆስፒታል በሕክምና ስትረዳ ከቆየች በኋላ ነው፡፡

ወ/ሮ ገነት ያረፈችው በቅርብ ሲንከባከቧት በነበሩት ባለቤቷ፣ ልጅዋ እናቷ፣ አክስቷና ሌሎችም የቤተሰብ አባላትና የቤተሰቡ ወዳጆች በተገኙበት ነው፡፡

ወ/ሮ ገነት ዘውዴና አቶ ሰሎሞን ክፍሌ በረዥሙ የትዳር ዘመናቸው አንዲት ልጅ አፍርተዋል፡፡
ወይዘሮ ገነት ዘውዴ
ወይዘሮ ገነት ዘውዴ
የወ/ሮ ገነት ዘውዴ ቤተሰቦች አርሊንግተን ቨርጂንያ፤ ኮሎምቢያ ፓይክ ላይ በሚገኘው የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አዳራሽ ውስጥ ዘመድ ወዳጅን እያስተናገዱ ሲሆን የፊታችን ሐሙስ፤ አፕሪል 3/2006 ዓ.ም ዋሽንግተን ዲ.ሲ በምትገኘው ርዕሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅድስት ማርያም ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የፀሎት ሥነ-ሥርዓት ተከናውኖ አስከሬኑ ወደ ትውልድ ሃገሯ ኢትዮጵያ በዚያው የሚሸኝ መሆኑን የቤተሰቡ አባላት ገልፀዋል፡፡

የቪኦኤ ባልደረቦች በተወዳጅዋ ጓደኛችን ወ/ሮ ገነት ዘውዴ ዕረፍት በእጅጉ አዝነናል፤ ለመላ ቤተሰብና ወዳጅ ዘመድ መፅናናትን እንመኛለን፡፡
XS
SM
MD
LG