11.01.2013
<h1>ኢትዮጵያ በጋዜጦች</h1><img src="http://amharic.voanews.com/App_Themes/VOA_am-ET/img/colorLogo.gif"/>የ United States መንግስት ለኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ ይሰጥ የነብረው ገንዘብ መቀነስ HIV ን በመታገል ረገድ ሀገሪቱ ያሳየችውን መሻሻል ሊጎዳ ይችላል ሲል IRIN የተባለው ስለ ሰብአዊ ጉዳዮች የሚዘግብና የሚተነትን የዜና አገልግሎት ጠቅሷል።<br /> <br /> በአለም አቀፍ የጤና ፖሊሲ በስራ አስኪያጅነት የሚመሩት በአለም አቀፍ የልማት ማእከልም አንጋፍ አባል የሆኑት አማንዳ ግላስማን PEPFAR በሚል አህጽሮት በሚጠራው የ United States ፕረዚዳንት የአስቸኳይ ግዜ የ AIDSን ህመም የማቃለል እቅድ መሰረት ለኢትዮጵያ ይሰጥ የነበረው ገንዘብ በ 79 ከመቶ ሊቀነስ ይችላል ሲሉ ጽፈዋል።<br /> <br /> የኢትዮጵያ ባለስልጣኖች የገንዘቡ መቀነስ ያሳሰባቸው መሆኑን ቢገልጹም የምንጠብቀው ነገር ነው ማለታቸውን IRIN ጠቁሟል።<br /> <br /> አንድ allAfrica.com ላይ የወጣ ጽሁፍ ደግሞ Sol Rebels ስለተባለው በኢትዮጵያ ስላለ የጫማ ፋብሪካ አፍላቂነትና ስኬት ዘግቧል። ይኸው የጫማ ፋብሪካ በያዝነው አመት በታይዋን ሁለተኛ የመሽጫ መደብር እንደሚከፍት አውስቷል።<br /> <br /> የጫማ ው ፋብሪካ የማ ይፈለጉ ነገሮችን መልሶ እጥቅም ላይ በማዋል ምቹ ጫማዎች የሚያመርት ሲሆን የተለያዩ በአፍላቂነት ላይ የተመሰረቱ የጫማ አይነቶችን በ 55 ሃገሮች ይሸጣል። በኢትዮጵያ እየመጠቁ ከሄዱት የንግድ ተቋማት አንዱ ለመሆን በቅቷል ሲል allAfrica.com ላይ የወጣው ጽሁፍ ጠቁሟል።<br /> <br /> npr ማለት National Public Radio የተባለው እውቅ ህዝባዊ ሬድዮ ጣብያም በአዲስ አበባ ስላለው የአህያ ማከምያ የጤና ጣብያ ዘግቧል።<br /> <div class="tag_image tag_audio_link" contenteditable="false" mode="audio|link|248801"> <img alt="" src="../../../img/spacer.gif" title="This is just placeholder, it will be replaced public site." />AMH-af-Ethiopia-Press-Review-1-11-13</div><link rel="canonical" href="http://amharic.voanews.com/content/article/1582221.html"/><meta name="syndication-source" content="http://amharic.voanews.com/content/article/1582221.html"/><img src="http://livetracker.voanews.eu/counter.lt?PageType=256&RecordId=1582221&SiteId=404&r=2014620013&it=0&pd=20130111191545&url=ArticleID1582221" alt="" style="border:none;" height="1" width="1">
Copy to clipboard Close