አዲስ አበባ —
“የውስጥ ችግራችሁን ፍቱ” በሚል የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የሰጠው ቀነ-ገደብ ዛሬ - ሰኞ፤ ጥር 4/2007 ዓ.ም ከመጠናቀቁ አንድ ቀን በፊት ትናንት የተካሄደው የመኢአድ ጠቅላላ ጉባዔ ቀደም ያሎ ውሣኔዎችን በማፅናት ተጠናቅቋል፡፡
ይህ ማለት ጥቅምት 28 እና 29 / 2007 ዓ.ም በተካሄደውና ምርጫ ቦርድ “አልቀበለውም” ባለው ጉባዔው የተላለፉ ውሣኔዎችን በድጋሚ አፅድቋል ማለት ነው፡፡
“የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ታዛቢዎቹን እንዲልክ ብንጋብዝም አልተገኙም” ሲሉ የፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ ማሙሸት አማረ ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡