<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?><rss version="2.0" xmlns:atom="http://www.w3.org/2005/Atom">     
    <channel>      
        <title>የራዲዮ መፅሔት - የአሜሪካ ድምፅ</title>     
        <link>https://amharic.voanews.com/z/3330</link>
        <description>ሬድዮ መጽሄት </description>
        <image>
            <url>https://amharic.voanews.com/Content/responsive/VOA/am-ET/img/logo.png</url>
            <title>የራዲዮ መፅሔት - የአሜሪካ ድምፅ</title>
            <link>https://amharic.voanews.com/z/3330</link>
        </image>
        <language>am</language>
        <copyright>2026 - VOA</copyright>   
        <ttl>60</ttl>        
        <lastBuildDate>Thu, 17 Sep 2026 14:47:23 +0300</lastBuildDate> 
        <generator>Pangea CMS – VOA</generator>        
        <atom:link href="https://amharic.voanews.com/api/zgtjte_i-r" rel="self" type="application/rss+xml" />
    		<item>
            <title>የዳያስፖራ ድርጅቶች ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የጻፉት ግልጽ ደብዳቤ</title>
            <description>በቁጥር ከደርዘን በላይ የሆኑ ዓለም አቀፍ ኢትዮጵያዊ የዳያስፖራ ድርጅቶች፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለሕዝብ የገቡትን ቃል አክብረው ዜጎችን ለመጠበቅ እና ቅሬታዎችን ለመፍታት ቆራጥ የማስተካከያ ርምጃዎች እንዲወስዱ ጠየቁ።


15 ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ድርጅቶቹ ጥያቄያቸውን ያቀረቡት፣ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በጻፉት ግልጽ ደብዳቤ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ እንደ ሀገር የመቀጠል ብሔራዊ ህልውናዋ አደጋ ላይ እንደሆነ አሳስበዋል፡፡


ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ግልጽ ደብዳቤ የጻፉትን የዳያስፖራ ድርጅቶችን ወክለው ያነጋገርናቸው፣ የአሜሪካ ኢትዮጵያውያን የሕዝብ ጉዳይ ኮሚቴ የቦርድ አባል እና ጸሐፊ አቶ ዮም ፍሥሃ እንደገለጹት፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ወሳኝ መፍትሔዎችን በማስተዋል መውሰድ እና በአፋጣኝ በሥራ ላይ ማዋል ይኖርባዋቸዋል፡፡ ይህን ማድረግ ካልቻሉ ግን፣ ኢትዮጵያ ከዚህ የበለጠ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ልትገባ እንደምትችል አሳስበዋል።


በደብዳቤው ዙሪያ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤትም ሆነ ከመንግሥት ጉዳዮች ኮምዩኒኬሽንስ ጽ/ቤት ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። ሆኖም ኮምዩኒኬሽንስ ጉዳዮች ጽ/ቤቱ በፌስቡክ ገፁ ላይ ለድርጅቶቹ የሰጠው ምላሽ በዘገባው ተካቷል።


/ስለ ደብዳቤው ከአሜሪካ ኢትዮጵያውያን የሕዝብ ጉዳይ ኮሚቴ የቦርድ አባል እና ጸሐፊ እንዲሁም አቶ ዮም ፍሥሓ ጋራ ተከታዩን ውይይት አድርገናል/




 

</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/7023584.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/7023584.html</guid>            
            <pubDate>Mon, 27 Mar 2023 22:09:26 +0300</pubDate>
            <category>ዜና</category><category>የራዲዮ መፅሔት</category><category>ኢትዮጵያ/ኤርትራ</category><author> voadigital@voanews.com (አሉላ ከበደ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/01000000-0aff-0242-b9bc-08db2ef6371c_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        <item>
            <title>በኢትዮጵያ ላይ የተሰናዳው የአሜሪካ ሴኔት ረቂቅ ህግ ነቃፊና ደጋፊዎች</title>
            <description>የዩናይትድ ስቴትስ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ &apos;በኢትዮጵያ ሰላምና ዲሞክራሲን እንዲሰፍን ለማበረታታት&apos; በሚል ርዕስ በኮሚቴው ሊቀመንበር ሴናተር ሮበርት ሜንዴዝ በቀረበው S. 3199 የተሰኘ ረቂቅ ህግ ዙሪያ ምስክሮችን ለመስማት ዛሬ ቀነ ቀጠሮ ይዞ ነበር። የኢትዮጵያ መንግስት ይህ ህግ ቢፀድቅ የሁለቱን ሀገሮች ግንኙነት እንደሚጎዳ ሲገልፅ፣ ሌሎች አካላት ደግሞ ኢትዮጵያ ወደ ሰላም እና ዲሞክራሲ እንድትሄድ የሚገፋፋ ነው በማለት ድጋፋቸውን ገልፀዋል።</description>
            <link>https://amharic.voanews.com/a/6498114.html</link> 
            <guid>https://amharic.voanews.com/a/6498114.html</guid>            
            <pubDate>Wed, 23 Mar 2022 22:51:00 +0300</pubDate>
            <category>ድምጽ</category><category>የራዲዮ መፅሔት</category><category>ጋቢና ቪኦኤ</category><author> voadigital@voanews.com (ስመኝሽ የቆየ)</author><enclosure url="https://gdb.voanews.com/02660000-0aff-0242-8371-08da0d05b029_w800_h450.jpg" length="0" type="image/jpeg"/>
        </item>		
        </channel></rss>