በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዞንጊ ደን


ወርዒ ለኸ
ወርዒ ለኸ

በትግራይ ዞንጊ ቀበሌ ከበረሃነት ወደ ደንነት ተለውጣለች፡፡

በትግራይ ክልል የአድዋ ሠንሠለታማ ተራሮች በመባል የሚታወቁት ከፍተኛ ቦታዎች በታሪክ በጥሩ መልኩ ቢታወሱም የተራቆቱ ስለመሆናቸው ግን እውነት ነው፡፡ በጦርነትና በድርቅ አደጋ ምክንያት አካባቢው የነበረውን የደን ሽፋን እያጣ መምጣቱ በግልፅ ይታያል፡፡

ይህም ሆኖ ግን የተራቆተውን መሬት እያዩ ብቻ ከማዘን ይልቅ በጥሩ ምሣሌነት የሚጠቀስ አካባቢ መመልከት ተመራጭነት ይኖረዋል፡፡

በትግራይ ማዕከላዊ ዞን የወርዕይ ወንዝን ያካለለው ሥፍራ ወርዒ ለኸ የሚል ስያሜ አግኝቷል፡፡

ከመቐለ በሓውዘን በኩል የነበለትን ከተማ በማለፍ ዕዳጋ ዓርቢ የሚባለው የወረዳው ማዕከል የሆነው ከተማ እስኪገባ ድረስ የአካባቢው የደን ሽፋን ገና በማቆጥቆጥ ላይ ይገኛል፡፡

የዕዳጋ ዓርቢን ከተማ አልፈው ወደ አድዋ በሚወስደው በረሃማ የገጠር መንደር ዞንጊ የሚባል ቦታ ግን በሚገርም ሁኔታ በደን ተሸፍኗል፡፡ በሃገር በቀል ደን የተሸፈነው ይህ ሥፍራ ከሌላው አካባቢ በተለየ ሁኔታ ነፋሻ ደሴት ሆኖ ይታያል፡፡ በአካባቢው ያለው ሙቀት በዚህች ቀበሌ ነፋሻ አየር ውስጥ ተውጦ ይቀራል፡፡

ለዝርዝሩ ዘገባውን ይመልከቱ፡፡

ተመሳሳይ ርእስ

XS
SM
MD
LG