በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የ‘ዞን-ዘጠኝ’ ብሎገሮች እሥራትና የተያያዙ ጉዳዮች


ዞን-9
ዞን-9

please wait

No media source currently available

0:00 0:13:06 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

ሦስት ጋዜጠኞችን ጨምሮ “አሸባሪ ውዥብር ነዝተዋል” በሚል ጥርጣሬ ፖሊስ ሰሞኑን በቁጥጥር ሥር ያዋላቸውን ዘጠኝ የኢንተርኔት አምደኞች (ብሎገሮች) ፍርድ ቤት አቅርቧል።

ፖሊስ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መፈቀዱም ተገልጿል።

በሌላ በኩል ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች፣ እንዲሁም ለጋዜጠኞች ደኅንነት ተቆርቋሪ ድርጅቶች ታሣሪዎቹ እንዲፈቱ የጠየቁባቸውን መግለጫዎች አውጥተዋል።

ታሣሪዎቹ ቤተሰብና ወዳጅ ዘመዶቻቸውም ሆኑ የሕግ አማካሪዎቻቸው እስካሁን እንዳላዩዋቸውም ተገልጿል።

በማዕከላዊ የወንጀል ምርመራ ጣቢያ አርብና ቅዳሜ በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው ያሉት የዞን-9 ዌብሳትይ አምደኞች ለመሆኑ እነማን ናቸው? ሦስቱ ጋዜጠኞችስ?

ለዝርዝሩ የያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
XS
SM
MD
LG