ሰሞኑን በምዕራብ ኢትዮጵያ ተቋርጦ ለቆየው የስልክ እና የኢንተርኔት አገልግሎት ምክንያት የሆኑ ችግሮች እየተወገዱና ጥገና እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮ-ቴሌኮም ኮርፖሬት ኮምዩኒኬሽንስ ኃላፊ አቶ አብዱራሂም ሞሐመድ አስታወቁ፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ለተራዘመ ጊዜ የተፈጠረና ስፋት ያለው አካባቢን ያካተተ የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ አለመፈጠሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ምሥክር ነጋሽ ተናግረዋል፡፡
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡