በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኃይሌ ገብረሥላሴ ውድድር አቆመ


በዛሬው ሳምንታዊ የስፖርት ፕሮግራማችን ኃይሌ ገብረ ሥላሴ መሰናበቱን፣ የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ሻምፒዮን እግር ኳስ ዋንጫ ውድድር መጀመሩን እና ሌሎች ዜናዎችን ይዘናል።

የዓለማችን ታላቁ አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ በ 15ኛው የኢትዮጵያ ታላቁ ሩጫ ላይ በይፋ ከአትሌቲክሱ ዓለም ተሰናበተ።

12 ሀገሮች የሚሳተፉበት የምሥራቅና መካከለኛው አፍሪካ ሻምፒዮን እግር ኳስ ዋንጫ ውድድር በኢትዮጵያ ተጀመረ። አስተናጋጅ ኢትዮጵያ በሩዋንዳ ብሄራዊ ቡድን 1 ለ 0 ተሸነፈች። በተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች የተጀመረው የሴካፋ ውድድር እስከ ህዳር 26 ቀን 2008 ዓም ይቆያል።

በስፔን ላ ሊጋ (La Liga) ባርሴሎና በእንግሊዙ ፕሪምየር ሊግ ደግሞ ሌስተር ሲቲ የደረጃ ሠንጠረዡን እየመሩ ናቸው።

ኃይሌ ገብረሥላሴ ውድድር አቆመ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:59 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

የኃይሌ ገብረ ሥላሴን የረጅም ርቀት ኃያልነትና የሩጫ ዘመኑ ትውስታዎች፣ ከዚህ በታች ያሉትን የፎቶ መድብሎችን ይመልከቱ።

XS
SM
MD
LG