በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አል-ሻባብ ቤተመንግሥቱን አጠቃ





please wait

No media source currently available

0:00 0:03:17 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

የአልቃይዳ ግብረአበር ናቸው የተባሉ ታጣቂዎች ሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ ውስጥ በፕሬዚዳንቱ ቤተመንግሥት - ቪላ ሶማሊያ ላይ ከፍተኛ አደጋ መጣላቸው ተዘግቧል፡፡

በጥቃቱ አንድ ከፍተኛ ባለሥልጣንን ጨምሮ ቢያንስ 17 ሰው ተገድሏል፡፡
በፕሬዚዳንቱ ላይ ጉዳት አልደረሰም፡፡

የዛሬው ጥቃት የአልሻባብ ጥቃት የተጣለው የሶማሊያ መንግሥትና የአፍሪካ ሕብረት ኃይሎች በቡድኑ ላይ አዲስ ጥቃት ለመክፈት እያቀዱ ባሉበት ወቅት ነው፡፡

ከዛሬው የጁምዐ ሶላት በኋላ አደጋ ጣዮቹ የቪላ ሶማሊያን ማለትም የፕሬዚዳንቱን ቤተመንግሥት ቅጥር ግቢ መግቢያ ከከበቡ በኋላ ወደ ውስጥ ዘልቀው ለመግባት በኃይል መሞከራቸውን እማኞች ተናግረዋል፡፡

ጥቃት አድራሾቹ ለማሳሳቻ የተጠቀሙበትን ወታደራዊ የደንብ ልብስ ለብሰው እንደነበርም የፀጥታ ባለሥልጣናት አመልክተዋል፡፡

የካናዳ ዜግነት የነበራቸው የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ኃላፊ ከተገደሉት መካከል እንደሚገኙ ታውቋል፡፡

ለጥቃቱ አል-ሻባብ ኃላፊነቱን ወስዷል፡፡

ለዝርዝሩና ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
XS
SM
MD
LG