በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የአሜሪካ ሴናተሮች “ኢትዮጵያ ውስጥ አለ” ያሉትን አፈና አወገዙ


የሜሪላንድ አንጋፊ ሴናተር ቤን ካርዲን /ፋይል ፎቶ/
የሜሪላንድ አንጋፊ ሴናተር ቤን ካርዲን /ፋይል ፎቶ/

የኢትዮጵያ መንግሥት በሲቪል ማኅበረሰብ ላይ እያካሄደ ነው ያሉትን አፈና እንደሚያወግዙ አሥራ ሁለት የዩናይትድ ስቴትስ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አባላት የሆኑ እንደራሴዎች ለምክር ቤቱ የውሣኔ ሃሣብ ረቂቅ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በሲቪል ማኅበረሰብ ላይ እያካሄደ ነው ያሉትን አፈና እንደሚያወግዙ አሥራ ሁለት የዩናይትድ ስቴትስ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አባላት የሆኑ እንደራሴዎች ለምክር ቤቱ የውሣኔ ሃሣብ ረቂቅ አቅርበዋል።

በሕገመንግሥት የተረጋገጡ መብቶቻቸውን እየተጠቀሙ ተቃዋሞዎቻቸውን በሰላማዊ መንገድ በሚገልፁ ሰልፈኞች፣ በጋዜጠኞችና በሲቪል ኅብረተሰብ አባላት ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት ግድያ የታከለበት የኃይል እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የገለፁ የዩናይትድ ስቴትስ የሕግ ወመሰኛ ምክር ቤት አባላት አድራጎቱን በብርቱ እንደሚያወግዙ ያሳወቁበትን የውሣኔ ሃሣብ ነው ይፋ ያደረጉት።

ሰነዱን ያዘጋጁትና የሴናተሮቹን ተቃውሞ የመሩት ዴሞክራቱ የሜሪላንድ አንጋፊ ሴናተር ቤን ካርዲን እና ሪፐብሊካኑ የፍሎሪዳው ሴናተር ማርኮ ሩቢዮ ናቸው።

ሪፐብሊካኑ የፍሎሪዳው ሴናተር ማርኮ ሩቢዮ /ፋይል ፎቶ/
ሪፐብሊካኑ የፍሎሪዳው ሴናተር ማርኮ ሩቢዮ /ፋይል ፎቶ/

የውሣኔ ሃሣቡን የያዘው ሰነድ የኢትዮጵያ የፀጥታ ኃይሎች ሲቪሎችን መግደላቸው በተገለፀበት በአሁኑ ሁኔታ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ሃገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር የገባውን የደኅንነት ውል መልሶ እንዲፈትሽ ይጠይቃል።

የሴናተሮቹ የውሣኔ ሃሣብ መግለጫ ሰነድ ረቂቅ አክሎም የኢትዮጵያ መንግሥት እየወሰዳቸው ያሉ የኃይል እርምጃዎችን እንዲያቆምና አጥፊዎች እንዲጠየቁ ያሳስባል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

የአሜሪካ ሴናተሮች “ኢትዮጵያ ውስጥ አለ” ያሉትን አፈና አወገዙ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:53 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG