በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዓለም መሪዎች የኦርላንዶውን ጅምላ ግድያ እያወገዙ ነው


ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ በኦርላንዶው ጥቃት ዙሪያ መግለጫ ሲሰጡ
ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ በኦርላንዶው ጥቃት ዙሪያ መግለጫ ሲሰጡ

በዩናይትድ ስቴትስ ፍሎሪዳ ክፍለ ግዛት ኦርላንዶ ከተማ በሀገሪቱ ታሪክ ከምንጊዜውም የከፋ በሆነው ጥቃት የመጪው ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ታሳቢ ዕጩዎችን ጨምሮ ከዓለም ዙሪያም ጸሎትና የሐዘን መግለጫ እየተሰማ ነው።የዓለም መሪዎችም ድጊቱን አውግዘዋል።

ለሰለባዎቹ ጸሎት እንዲካሄድ፥ ቤተሰቦችንም ማጽናናት እንደሚያስፈልግ ለዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዘዳንትነት በመወዳደር ላይ የሚገኙ እጩዎች አሳስበዋል።

የዲሞክራቲክ ፓርቲው ታሳቢ ዕጩ ሂላሪ ክሊንተን ለሲ.ኤን.ኤን ቴለቪዢን በሰጡት ቃል"ሀገራችንን በራሳቸው ተነሳሽነት ጥቃት ከሚያደርሱት መጠበቅ አለብን” ብለዋል። "ሁላችንም አሜሪካዊያን ሽብርተኝነትና ሌላም ሁከተኛ ተግባራትን አብረን እንደ አንድ አካል መታገል የምንችል መሆናችንን አጋጣሚው ያስገነዝበናል” ሲሉም አክለዋል።

የሪፐብሊካን ፓርቲው ተቀናቃኛቸው ዶናልድ ትረምፕ ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማና ሊሎች ዲሞክራቶች ሙስሊም የሆኑ ሽብርተኞችን ጽንፈኛ ብለው ለመጥራት ፈቃደኛ አይደሉም ብለው ለሚሰነዝሩት ውንጀላ ክሊንተን ምላሽ ሰጥተዋል። “እኔ ቃሉን መጥራት አልፈራም ፈቃደኛ የማልሆነው አንድን ሃይማኖት እንዳለ እንደጭራቅ ስሎ ጦርነት ማወጅን ነው” ብለዋል።

ባልደረቦቻችን Wayne Lee እና Smita Nordwall ያጠናቀሩት ዘገባ አለ።

ዝርዝርሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ።

የዓለም መሪዎች የኦርላንዶውን ጅምላ ግድያ እያወገዙ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:08 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG