በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የ 2013 DV ሎተሪ መስከረም 23 ቀን 2004 አም እንደሚጀመር ተገለጸ


የ 2013 የአሜሪካ ዳይብቨርሲቲ ቪዛ ሎተሪ DV መስከረም 23 ቀን 2004 አም እንደሚጀመር በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ይፋ አደረገ።አመልካቾች እንዳይታለሉ የኤምባሲው የኮንስለር ባለስልጣናት ማሳሰብያ ሰጡ።

“ኦፊሴላዊው የ DV መርሀ-ግብር የማይከፈልበትና በነጻ የሚሰጥ መሆኑን ሰዎች ሊያውቁት ይገባል። እና አንድ ሰው ለዚህ ፕሮግራም ቢመረጥ ከ UnitedStates መንግስት ምንም አይነት ደብዳቤ አያገኝም። ወይም አይላክለትም።ኢ-መይልም ከአሜሪካ መንግስት አያገኝም። ማንኛውም ሰው ማድረግ ያለበት ማመልከቻውን ካስገባ በኋላና ለማመልከቻው የተረጋገጠለትን ቁጥር ካገኘ በኋላ የማመልከቻዋን ሁኔታ ወይንም የደረሰበትን ሁኔታ በድረ-ገጹ መከታተል ብቻ ነው።” ሲሉ አዲስ አበባ የሚገኘው የ United States ኤምባሲ ዋና ኮንስለር ስካት ሪድማን አስገንዝበዋል።

ተመሳሳይ ርእስ

XS
SM
MD
LG