በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ጥር ወር ጀምሮ ከ5 ሺሕ በላይ ሶማሊያውያን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸው ተገለፀ


እአአ ከጥር 2017 ጀምሮ ከ5 ሺሕ በላይ ሶማሊያውያን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

እአአ ከጥር 2017 ጀምሮ ከ5 ሺሕ በላይ ሶማሊያውያን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

ይሕም ሆኖ በጎረቤት ሶማሌያ የተከሰተው ኮሎራም ሆነ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የታየው የአጣዳፊ ትውከትና ተቅማጥ በሽታ እየመጡ ባሉት ስደተኞች እና በካምፖቹ ውስጥ አለማጋጠሙን በአዲስ አበባ የኮሚሽኑ ቃል አቀባይ ገልፀዋል፡፡

የኮሚሽኑ ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ክሱት ገ/እግዜብሄር እንደገለፁት፣ የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሺነር ሰሞኑን ይፋ ባደረገው መረጃ እንደሚያሳየው እአአ ከግንቦት 1/2017 ጀምሮ ባሉት በአሥራ አምስት ቀናት ብቻ 1 መቶ 75 ሶማሌያውያን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ጥር ወር ጀምሮ ከ5 ሺሕ በላይ ሶማሊያውያን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸው ተገለፀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:52 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG