በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የተ.መ.ድ. አመጽ ለመታደግ የሚያስችል መግለጫ አወጣ


የአል-ሸባብ ታጣቂ
የአል-ሸባብ ታጣቂ

የተ.መ.ድ. የልማት ፕሮግራም የሽብርተኛነት አመጽ ለመታደግ የሚያስችል ያወጣው መግለጫ።

የተ.መ.ድ. የልማት ፕሮግራም (UNDP)የአፍሪቃ ክልላዊ ቢሮ፣ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ የአፍሪቃን አገሮች እየተስፋፋ ከመጣው የሽብርተኛነት አመጽ ለመታደግ የሚያስችል መርሓ-ግብር ይፋ አደረገ።

የልማት ፕሮግራሙ (UNDP) የአፍሪቃ ፕርግራም ድሬክተር አብዱላየ ማር ድየ (Abdoulaye Mar Dieye) በዚህ ይፋ በተደረገው መርሓ-ግብር የመክፈቻ ከፍተኛ ውይይት ላይ ሲናገሩ፣ አያሌ የአፍሪቃ ወጣቶችን ከአምራችነት ሕይወት ወደ ሽብርተኛነት እንዲገቡ የሚያደርገውን ሁኔታ ለመገደብ በብርቱ መጣር ይኖርብናል ብለዋል።

የዚህ ልማት-ተኮር የሆነው ከፍተኛ መርሓ-ግብር ተባባሪ አስተናጋጅ፣ በተመድ የስዊድን ቋሚ ሚሽን መሆኑም ታውቋል።

አመጽ የተቀላቀለበት አክራሪነት፣ በመላ አህጉሪቱ ላይ ከፍተኛ ማኅበራዊና ኤክኖሚያዊ አንደምታ እንዳስከተለ ይታወቃል።

እንደ ናይጄሪያው ቦኮ ሀራም፣ እንደ ሲማልያው አል-ሻባብ የመሳሰሉት ቡድኖች፣ የክልሉን ሰላምና አንድነት በማናጋት ላይ ብቻ ሳይወሰኑ፣ ለብዙ መቶ ሺህ ሕዝብ ከቤት ንብረቱ መፈናቀልም ሚክናት ሆነዋል።

የተ.መ.ድ.አመጽ ለመታደግ የሚያስችል መግለጫ አወጣ
please wait

No media source currently available

0:00 0:01:16 0:00

XS
SM
MD
LG