በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዚካ ወረርሽኝ ጥናትና ምርምር ቫይረሱ በተገኘባት ዑጋንዳ


 የዑጋንዳው የቫይረስ ጥናት ማዕከል ከፍተኛ የጥናት ባለ ሞያ ጁልየስ ሉትዋማ
የዑጋንዳው የቫይረስ ጥናት ማዕከል ከፍተኛ የጥናት ባለ ሞያ ጁልየስ ሉትዋማ

“ቫይረሱ ተለይቶ የታወቀው እዚህ ነው። ሌሎች በርካታ የጥናት ሥራዎችም እዚሁ ጫካ ውስጥ ነው የተካሄዱት። እንደተገለጸው እነኚህ ሁሉ የጥናት ሥራዎች እዚህ ሥፍራ ባይካሄዱ ኖሮ፤ ምናልባትም ቫይረሱ እስካሁንም ባልታወቀ፤ አለያም እንደ አዲስ በሽታ በተወሰደ ነበር። በመሆኑም ጥሩነቱ ቀድሞ የተታወቀ ቫይረስ በመሆኑ እንዲህ እንዳሁኑ በወረርሽኝ መልክ ሲከሰት፤ የግድ ከዜሮ መጀመር አይኖርብንም።” የዑጋንዳው የቫይረስ ጥናት ማዕከል ከፍተኛ የጥናት ባለ ሞያ ጁልየስ ሉትዋማ

ብራዚል በአንድ በኩል በበጋው ወራት የሚጀምረውን የኦሎምፒክ ለማስተናገድ እየተሰናዳችና በሌላ በኩልደግሞ በአገሪቱ የሚታየውን የዚካ ቫይረስ ሥርጭት የደቀነውን ፈተና ለመቋቋም ጥረት በማድረግ ላይ ባለችበት ባሁኑወቅት፤ ዓለም በተለይም ደግሞ ሥርጭቱ የተስፋፋባቸውን የደቡብ አሜሪካ አገሮች ወረርሽኙ በፈጠረው ሥጋትየተያዙ ይመስላል።

ጸጥታ የሰፈነበት ሥፍራ ነው። ቅጠሎች ሲረግፉ፥ ንፋሱ ሲውለበለብና ዝንጀሮዎች ከዛፍ ዛፍ ሲዘሉ ጎልቶ ይሰማል።ከርቀት ሲያዩት ከየትኛውም ደንና ጫካ የተለየ የማይመስል ሥፍራ!

“ቫይረሱ ተለይቶ የታወቀው እዚህ ነው። ሌሎች በርካታ የጥናት ሥራዎችም እዚሁ ጫካ ውስጥ ነው የተካሄዱት።”
የዑጋንዳው የቫይረስ ጥናት ማዕከል ከፍተኛ የጥናት ባለ ሞያ ጁልየስ ሉትዋማ

እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር በ1947ዓ.ም. የዑጋንዳ የቫይረስ ጥናት ማዕከል ተመራማሪዎች የቢጫ ወባቫይረስን ለመለየት የምርምር ሥራ በማካሄድ ላይ ሳሉ ጫካውን መኖሪያቸው ባደረጉ ዝንጀሮዎች ደም ውስጥ የሌላበጊዜው ያልታወቀ ቫይረስ ዝርያ ያገኙበትን ሰላሳ ሰባት ሜትሮች ቁመት ያለውን ግዙፍ ማማ የሚያገኙት። አዎን ዛሬ የዚህ ሁሉ ሥጋት መንስኤ ለመሆን የበቃው ዚካ ገና ትላንት የታወቀ አዲስ ክስተትም አይደለም። በዚያ በራቀዘመንና ሥፍራ የተገኘ እንጂ።

የዑጋንዳው የቫይረስ ጥናት ማዕከል ከፍተኛ የጥናት ባለ ሞያ ጁልየስ ሉትዋማ
የዑጋንዳው የቫይረስ ጥናት ማዕከል ከፍተኛ የጥናት ባለ ሞያ ጁልየስ ሉትዋማ

መጠሪያ ሥያሜውንም ከዚሁ ጫካ ነው ያገኘው። ከዚካ ጫካ። እናም ከበርካታ አሥርታት በኋላ ዛሬ በብራዚልና በተቀሩት የምዕራቡ ዓለም አካባቢዎች ድንገት የጊዜው አሳሳቢ ፈተናሆኖ ብቅ አለ። ከበርካታ አሥርታት በፊት ቫይረሱ ለመጀመሪያ ጊዜ ከተለየና በታወቀባት ዑጋንዳ ተመራማሪዎች ለጥናቱየሚያስፈልገው በጀት ከተገኘ ለቀጣይ ምርምር ዝግጁ መሆናቸውን ይናገራሉ።

የዚካ ወረርሽኝ ጥናትና ምርምር ቫይረሱ በተገኘባት ዑጋንዳ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:54 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG