በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ማሊ ውስጥ ከአይቮሪ ኮስት የሽብር ጥቃት ጋር በተያያዘ ሁለት ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ባለሥልጣት አስታወቁ


ፖሊስ ወደ ግራንድ ባሳም አይቮሪ ኮስት እያመሩ እ.አ.አ. 2016
ፖሊስ ወደ ግራንድ ባሳም አይቮሪ ኮስት እያመሩ እ.አ.አ. 2016

​​ሌሎች 15 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር እንደሚገኙም፣ የአካባቢው ዐቃብያነ -ህግ አስታውቀዋል።

ማሊ ውስጥ ባለፈው ወር ቢያንስ 19 ሰዎች ከተገደሉበት የሽብር ጥቃት ጋር በተያያዘ ከአል-ቃዒዳ ጋር ንክኪ አላቸው የተባሉ ሁለት ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ባለሥልጣት አስታወቁ።

የፖሊስ መግለጫ እንዳመለከተው ሰዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት ባለፉት 48 ሰዓታት ሰሜናዊ ማሊ ውስጥ ሲሆን ይህም፣ ግራንድ ባሳም (Grand-Bassam) በተባለው የአይቮሪ-ኮስቱ መዝናኛ ስፍራ በሚገኙ ሦስት ሆቴሎች ውስጥ የደረሰው ጥቃት በተካሄደ በ3ኛው ወር መሆኑ ነው።

ለሽብርተኞቹ እንደ ሾፌር ሆኖ ወደ አይቮሪ-ኮስት ያመጣቸው ኦልድ መሐመድ (Ould Mohamed) የተባለው ከተጠርጣሪዎቹ አንደኛው ሲሆን፣ የጥቃቱ ዋነኛ አቀነባባሪ መሆኑንም፣ የፈረንሳይ ዜና አውታር ዘግቧል።

ሌሎች 15 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር እንደሚገኙም፣ የአካባቢው ዐቃብያነ -ህግ አስታውቀዋል።

ታጣቂዎች በአይቮሪ ኮስት ግራንድ ባሳም መዝናኛ ስፍራ ላይ ዛሬ ጥቃት ፈጽመዋል
please wait

No media source currently available

0:00 0:00:33 0:00

XS
SM
MD
LG