በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሚነሶታ ፖሊስ፡ ሁለት ኢትዮጲያውያን ሞቱ ፣ አንዱ ደግሞ የከፋ ጉዳት ደርሶበታል


ፖሊስ
ፖሊስ

ሁለት ወጣቶች በሚንያፖሊስ ከተማ፣ ሚነሶታ መኪና ውስጥ በተኩስ ተገድለው መገኘታቸውንና ሶስተኛው ወጣት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት በሆስፒታል እርዳታ እየተደረገለት መሆኑ ታውቋል።

ባለፈው እሁድ እአአ ሕዳር 22 2015 ምሽት ላይ ሁለት ወጣቶች በሚንያፖሊስ ከተማ፣ ሚነሶታ መኪና ውስጥ በተኩስ ተገድለው መገኘታቸውንና ሶስተኛው ወጣት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት በሆስፒታል እርዳታ እየተደረገለት መሆኑን የሚንያፖሊስ ከተማ ፖሊስ ጆን አልደር (John Elder) ለCBS ቴለቪዥን ገልጿል።

"የከተማው ፖሊሶች በወቅቱ ቦታው ላይ የነበሩ ሰዎችን እያነጋገሩና ጉዳዮን እየመረመሩ ሲሆን፣ ተጠርጣሪዎቹ ወድያው በእግር እንደሸሹና እስካሁንም እንዳይልተያዙ" ጆን አልደር ገልጸዋል። የቪድዮ ቃለ ምልልሱን ከዚህ ፋይል ይመልከቱ።

የሚንያፖሊስ ከተማ ፖሊስ ባጅ

ፖሊስ የነዚህን ወጣቶች ማንነት ይፋ ያላደርገ ሲሆን የከተማይቱ ነዋሪዎች ሦስቱን ወጣቶች ኦሮሞ መሆናቸውን ይናገራሉ። በትናንትናው ዕለት ፖሊስ መግለጫ ሲሰጥ፣ በስፍራው የተገኙና የብራየን ኮይል ኮሚዩኒቲ ዳይረክተር (Brian Coyle Community Director) የሆኑት አቶ አማኖ ዱቤ "እነዚህ ልጆች ሦስቱም ኦሮሞች ናቸው የኮሌጅ ተማሪዎችም ነበሩ። የሚንያፖሊስ ፖሊስ፣ ወጣቶቹ ሙስሊም ስለሆኑና በቶሎ መቀበር እንዳለባቸው ስለምናውቅ፣ ምርመራውን በቶሎ ለመጨረስ እንሞክራለን ብለውናል" ብለዋል።

ዝርዝሩን ለመስማት ከዚህ በታች ያለውን የድምጽ ፋይል ያዳምጡ።

በሚነሶታ ሁለት ኢትዮጲያውያን ሞቱ ፣ አንዱ ደግሞ የከፋ ጉዳት ደርሶበታል
please wait

No media source currently available

0:00 0:01:31 0:00

XS
SM
MD
LG