በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ሁለት ኢትዮጵያውያን ከ30,000 ዶላር በላይ ለዓለም ምግብ ፕሮግራም አስረከቡ


ዶ/ር አበበ ሃረገውይንና አብርሃም ተፈሪ ዲሲ በሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP)ጽ/ቤት ከ30,000 ዶላር በላይ የሰበሰቡትን ገንዘብ ሲያስረክቡ
ዶ/ር አበበ ሃረገውይንና አብርሃም ተፈሪ ዲሲ በሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP)ጽ/ቤት ከ30,000 ዶላር በላይ የሰበሰቡትን ገንዘብ ሲያስረክቡ

ሁለት ኢትዮጵያውያን ዳያስፖራ ከ30,000 ዶላር በላይ የምግብ እጥረት ለደረሰባቸው ወገኖች እርዳታ ሰብስበው በዛሬው እለት ገንዘቡን ለዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ለተራቡ ወገኖች እንዲያደርስ አስረክበዋል።

ጎ-ፈንድ-ሚ ወይም (GoFundMe) በግርዱ ወደ አማርኛ ሲመለስ፤ “ድጋፍህን ስጠኝ፤” በሚል ስያሜ በሚታወቀውና በሚልዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ከ1 ቢልዮን ዶላር በላይ በ 365 ቀናት ውስጥ ሊሰበስቡ የሚችሉበት ድረ-ገጽ ነው።

ሁለት ኢትዮጵያውያን፣ ዶ/ር አበበ ሃረገውይንአብርሃም ተፈሪ ድረ-ገጹን በመጠቀም በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ የምግብ እጥረት ለደረሰባቸው ወገኖች እርዳታ አሰባስበዋል። እስከ ዛሬ ከ30,000 ዶላር በላይ የሰበሰቡ ሲሆን፣ በዛሬው እለት ገንዘቡን ለዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ለተራቡ ወገኖች እንዲያደርስ አስረክበዋል።

ሳሌም ሰለሞን በርክክቡ ላይ ተገኝታ ያጠናቀረችውን ቃለ-ምልልስ ከዚህ በታች ካለው የድምጽ ፋይል ያዳምጡ።

ሁለት ኢትዮጵያውያን ከ30,000 ዶላር በላይ ለዓለም ምግብ ፕሮግራም አስረከቡ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:17 0:00

በተጨማሪም የቪድዮ ፋይሉን በመጫን የኢትዮጵያኑን መልእክት ይመልከቱ።

ሁለት በዳያስፖራ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከ30,000 ዶላር በላይ ለዓለም ምግብ ፕሮግራም አስረከቡ
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:08 0:00

የፎቶ መድብሎቻችንንም ከዚህ በታች ካለው ፋይል ይመልከቱ።

XS
SM
MD
LG