በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

26ኛው የዓለም ፀረ-ኤድስ ዘመቻ ቀን በኢትዮጵያ


የዓለም ፀረ-ኤድስ ዘመቻ ቀን
የዓለም ፀረ-ኤድስ ዘመቻ ቀን

ኢትዮጵያ 26ኛውን የዓለም የኤድስ ቀን ጋምቤላ ከተማ ላይ ትናንት በተካሄደ ይፋ ሥነ-ሥርዓት አስባለች፡፡

የዓለም የኤድስ ቀን
የዓለም የኤድስ ቀን

please wait

No media source currently available

0:00 0:23:11 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

ኢትዮጵያ 26ኛውን የዓለም የኤድስ ቀን ጋምቤላ ከተማ ላይ ትናንት በተካሄደ ይፋ ሥነ-ሥርዓት አስባለች፡፡

የኤችአይቪ ሥርጭት መጠን ኢትዮጵያ ውስጥ 1 ነጥብ 2 ከመቶ ሲሆን የጋምቤላ ሥርጭት መጠን ግን 5 ነጥብ 8 መሆኑ ተገልጿል፡፡

በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ኤችአይቪ በደሙ ውስጥ የሚገኘው ሰው ቁጥር ከ750 ሺህ እስከ 800 ሺህ እንደሚደርስም ተነግሯል፡፡

የዓመቱ የኤድስ ቀን መሪ ቃል “አንድም ሰው በኤችአይቪ እንዳይያዝ፣ እንዳይገለል እና እንዳይሞት ኃላፊነታችንን እንወጣ” የሚል ነው፡፡

ኤችአይቪ ዓለምአቀፍ ወረርሽኝ ከሆነበት ጊዜ አንስቶ ባለፈው ወደ አርባ ዓመታት የሚጠጋ ጊዜ ውስጥ ወደ ሰማንያ ሚሊየን ሰው ለኤችአይቪ የተጋለጠ ሲሆን ከመካከሉም ግማሽ ያህሉ በኤድስ ምክንያት አልፏል፡፡

ዓለም ዛሬ “ዘመቻ ዜሮ”ን እያካሄደ ሲሆን በመጭዎቹ 15 ዓመታት ውስጥ ኤድስን ለማቆም እየተንቀሣቀሰ ይገኛል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

XS
SM
MD
LG