በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ዶናልድ ትራምፕ በአስተዳደራቸው የሚካተቱ ባለሥልጣናትን ለመለየት እየሠሩ ነው


ተመራጩ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ
ተመራጩ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ

በዩናይትድ ስቴትስ ተመራጩ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአስተዳደራቸው ውስጥ የሚካተቱትን ባለሥልጣናት ለመለየት እየሠሩ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የቀድሞው የኒውዮርክ ከተማ ከንቲባ ሩዲ ጊሌአኒ ቀጣዩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለመሆን ቀዳሚ ዕጩ መሆናቸውን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገልፀዋል።

ጊሊአኒ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግነት ሥራ ልምድ ቢኖራቸውም በውጭ ጉዳዮች ፖሊሲ ጉዳይ ግን ከቀደሙት ባለሥልጣናት ጋር አይመጣጠኑም።

ጊሊአኒ በዶናልድ ትራምፕ የምረጡኝ ዘመቻ ወቅት፤ ጠንካራ ደጋፊ እንደነበሩ ይታወቃል።

በሌላም በኩል በዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ሊካተቱ ይችላሉ የሚባሉት፤ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የቀደሞው የዩናይትድ ስቴትስ አምባሣደር ጆን ቦልተን ናቸው።

XS
SM
MD
LG