በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ዩናይትድ ስቴትስ የኢትዮጵያ መንግሥት በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የወሰደው የሀይል እርምጃ መፍትሄ አይደለም አለች


በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መስርያ ቤት የዲሞክራሲ የሰብዓዊ መብቶች እና የሥራ ጉዳይ ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሎስኪ
በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መስርያ ቤት የዲሞክራሲ የሰብዓዊ መብቶች እና የሥራ ጉዳይ ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሎስኪ

በኢትዮጵያ እየተወሰዱ ያሉት የሀይል እምጃዎችና ሌሎቹ ለሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ መፍትሄ ሊሆኑ አይችሉም ሲሉ በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ረዳት ሚኒስቴር ቶም ማሎንስኪ አስታወቁ።

ረዳት ሚኒስትሩ እንዳሉት የፀጥታ ሀይሎች ከመጠን ያለፈ ሀይል መጠቀም በርካታ ሰዎችን መግደል እና ማቁሰል እንደዚሁም በሺዎች የሚቆጠሩ ማሰር ቀጥለዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ሰላማዊ ሰልፎቹ ሰላማዊ አልነበሩም ብሏል።

ከሰልፎቹ ጥቂቶቹ ለብጥብጥ መሳርያነት ጥቅም ላይ ውለው ይሆናል ያሉት በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መስርያ ቤት የዲሞክራሲ የሰብዓዊ መብቶች እና የሥራ ጉዳይ ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሎስኪ አብዛኛዎቹ የሰልፉ ተሳታፊዎች ግን በኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት የሰፈረውን ሃሳብ የመግለፅ መብት የተጠቀሙ እንደነበር እናምናለን ብለዋል።

ኢትዮጵያ የውጭ ስጋቶች እንዳሉባት እንደሚረዱም ጠቅሰዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

ዩናይትድ ስቴትስ የኢትዮጵያ መንግሥት በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የወሰደው የሀይል እርምጃ መፍትሄ ኣይደለም አለች
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:49 0:00

XS
SM
MD
LG