በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አንዳርጋቸውን “ለማስለቀቅ ሪፕሪቭ እየጣረ ነው”


ማያ ፎ፤ የሪፕሪቭ የሞት ቅጣት ጉዳዮች ተከታታይ ቡድን ዳይሬክተር
ማያ ፎ፤ የሪፕሪቭ የሞት ቅጣት ጉዳዮች ተከታታይ ቡድን ዳይሬክተር
አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ - ፎቶ ከኢንተርኔት የተገኘ
አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ - ፎቶ ከኢንተርኔት የተገኘ

please wait

No media source currently available

0:00 0:12:21 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

ዓለምአቀፍ ጉዞ ላይ ሳሉ ከየመን ዋና ከተማ ሰንዓ አይሮፕላን ጣቢያ ተጠልፈው ወደ ኢትዮጵያ የተወሰዱትና አሁን እሥር ላይ የሚገኙት የቀድሞ የግንቦት ሰባት ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ እንዲለቀቁ ለማድረግ እየጣረ መሆኑን ሪፕሪቭ የሚባለው ድርጅት ዳይሬክተር አስታውቀዋል፡፡

ማያ ፎ፤ የሪፕሪቭ የሞት ቅጣት ጉዳዮች ተከታታይ ቡድን ዳይሬክተር
ማያ ፎ፤ የሪፕሪቭ የሞት ቅጣት ጉዳዮች ተከታታይ ቡድን ዳይሬክተር

የሞት ፍርደኞችን ለማገዝና ለመደገፍ የሚሠራው ዓለምአቀፍ ግብረሠናይ ድርጅት ዳይሬክተር ማያ ፎ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል “አንዳርጋቸው የታሠሩት ሕገወጥ በሆነ መንገድ ነው፤ ወደ ኢትዮጵያ ተጠልፈው የተወሰዱትም በሕገወጥ ሁኔታ ነው ብለን ነው የምናምነው” ብለዋል፡፡

ሪፕሪቭ
ሪፕሪቭ

የአቶ አንዳርጋቸውን ጉዳይ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዘፈቀደ እሥራቶች ተከታታይ ቡድን እየተከታተለ መሆኑንና እሥራቱ በዘፈቀደ የተፈፀመና ሕገወጥም መሆኑን በመጠቆም እንዳለቀቁ መጠየቁን፣ የድርጅቱ የሥቃይ አያያዝ ወይም ቶርቸር ጉዳዮች ልዩ ራፖርተርም ስለዚሁ ጉዳይ ለኢትዮጵያም ለእንግሊዝ መንግሥትም አንዳርጋቸው በሥቃይ የመያዝ አደጋ ስላለባቸው እዚያ ተይዘው መቆየት እንደሌለባቸው አሳስበው ደብዳቤ መፃፋቸውንና የአፍሪካ ኅብረትም ጉዳዩን እየተከታተለው መሆኑን ማያ ፎ ገልፀዋል፡፡

ለተጨማሪ ዝርዝር የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

XS
SM
MD
LG