በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኦብነግ “ተጠልፈው ነበር” ያላቸው ተደራዳሪዎቹ መለቀቃቸውን አስታወቀ


የኦብነግ አርማ /ፎቶ - ከዊኪፔድያ የኢንተርኔት ኢንሳይክሎፔድያ የተገኘ/
የኦብነግ አርማ /ፎቶ - ከዊኪፔድያ የኢንተርኔት ኢንሳይክሎፔድያ የተገኘ/

የኢትዮጵያ መንግሥት ባለፈው ዓመት ከናይሮቢ አፍኖ ወስዷቸው ነበር ያላቸው ሁለት ተደራዳሪዎቹ ከትናንት በስተያ - ሰኞ መለቀቃቸውን የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጭ ግንባር - ኦብነግ አስታውቋል፡፡

የኦብነግ አርማ /ፎቶ - ከዊኪፔድያ የኢንተርኔት ኢንሳይክሎፔድያ የተገኘ/
የኦብነግ አርማ /ፎቶ - ከዊኪፔድያ የኢንተርኔት ኢንሳይክሎፔድያ የተገኘ/

please wait

No media source currently available

0:00 0:07:49 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

የኢትዮጵያ መንግሥት ባለፈው ዓመት ከናይሮቢ አፍኖ ወስዷቸው ነበር ያላቸው ሁለት ተደራዳሪዎቹ ከትናንት በስተያ - ሰኞ መለቀቃቸውን የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጭ ግንባር - ኦብነግ አስታውቋል፡፡

እነዚህ ከአንድ ዓመት ከአራት ወራት በኋላ የተለቀቁት ሁለቱ የግንባሩ ባለሥልጣናት ሱሉብ አህመድ እና አሊ ሁሴን የሚባሉ ሲሆኑ ሁለቱም አሁን ከቤተሰቦቻቸው ጋር በጤና እንደሚገኙ የግንባሩ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የኢንፎርሜሽን ቢሮ ኃላፊ ማምሻውን ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡

ሰዎቹ የተለቀቁት በኬንያ መንግሥትና በሌሎችም ዓለምአቀፍ ጥረቶች መሆኑን አቶ ሃሰን ገልፀዋል፡፡

አንድ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣን ቀደም ሲል ለቪኦኤ ሰጥተውት በነበረ መግለጫ ሰዎቹ እጃቸውን በገዛ ፍቃዳቸው ሰጡ እንጂ በክሡ ላይ እንደሚባለው አፈና ወይም ጠለፋ አልተካሄደባቸውም ብለው ነበር፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

XS
SM
MD
LG