በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኦሮምያ ክልል በርካታ ሰዎች እየታሰሩ ነው ተባለ


በኦሮሚያ ክልል በርካታ ሰዎች በምሸት እየተያዙና ወዳልታወቀ ቦታ እየተወሰዱ ነው ሲል የኦሮሞ ፈደራሊስት ኮንግረስ አስታወቀ።

መንግሥት ደግሞ ከሕግ ውጪ ማንም የታሰረ ሰው የለም ብሏል።

የኦሮሞ ፈደራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ሙላቱ ገመቹ ለአሜሪካ ድምፅ እንዳስረዱት በኦሮምያ ክልል የሚካሄደው ማሰር እና ማሳደድ ቀጥሏል።በተለይ በምሽት የሚወሰዱት ሰዎች የት እንደታሰሩ እንኳን ለማወቅ እንዳልተቻለ አብራርተዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በቅርቡ በኦሮምያ ክልል ከተካሄደ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ከታሰሩ ሰዎች ከአንድ ሺሕ በላይ የሚሆኑ መፈታታቸውን መረጃ እንዳላቸው የኦሮሞ ፈደራሊስ ኮንግረስ አቶ ሙላቱ ገመቹ አስታውቀዋል።

አቶ ሙላቱ ገመቹ የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር
አቶ ሙላቱ ገመቹ የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር

አንድም ሰው ሲፈታ ደስ ይለናል ያሉት ምክትል ሊቀ መንበሩ መንግሥት የቀሩትንም በሙሉ እንዲፈታ ጥሪ አቅርበዋል።

በክልሉ የተካሄደውን የተቃውሞ እንቅስቃሴ ተከትሎ የታሰሩት ሰዎች ቁጥር ወደ 10,000 ሊጠጋ እንደሚችልም ጠቁመዋል።

ብዙ ሺህ ታሳሪዎች በተለያዩ ቦታዎች እንደሚገኙም ምክትል ሊቀመንበሩ አብራርተዋል።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

በኦሮምያ ክልል በርካታ ሰዎች እየታሰሩ ነው ተባለ
please wait

No media source currently available

0:00 0:09:04 0:00

XS
SM
MD
LG