በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኦፌኮ ከፍተኛ የአመራር አባላት በማረሚያ ቤት ከፍተኛ በደል ይደርስብናል አሉ


እነ አቶ በቀለ በማረሚያ ቤት ስድብ ማስፈራራትና ሌሎችም ከፍተኛ ተጽኖዎች እንደተፈጸመባቸው ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቅርበዋል።

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ከፍተኛ የአመራር አባል አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ 22 በሽብር የተጠረጠሩ ተከሳሾች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ቀረቡ።

እነ አቶ በቀለ በማረሚያ ቤት ስድብ ማስፈራራትና ሌሎችም ከፍተኛ ተጽኖዎች እንደተፈጸመባቸው ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቅርበዋል። የማረሚያ ቤቱ ተወካይ አቤቱታውን አስተባብለዋል። ተከሳሾቹ በቀረበባቸው ክስ ላይ ያላቸውን አስተያየት እንዲሰጡ ለሌላ ጊዜ ተቀጥረዋል።

የድምጽ ፋይሉን በመጫን ሙሉውን ዘገባ ከመለስካቸው አመሃ ያድምጡ።

የኦፌኮ ከፍተኛ የአመራር አባላት በማረሚያ ቤት ከፍተኛ በደል ይደርስብናል አሉ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:42 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

33 ሰዎች የኦሮሞ ነፃነት ግንባርን ድርጅታዊ ህዋስ በመመሥረትና በአሸባሪነት ተከሰሱ

የኢትዮጵያው ፌዴራል ዐቃቤ ህግ፣ 33 ሰዎችን በአገር ውስጥ የኦሮሞ ነፃነት ግንባርን (የኦነግን) ድርጅታዊ ህዋስበመመሥረት፣ በመምራትና አባላት በመሆን የሽብር ወንጀል ፈጽመዋል ሲል፣ በፌዴራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት19ኛ ወንጀል ችሎት ክስ መሠረተባቸው። ፍርድ ቤቱም፣ ተከሳሾቹ መልስ እንዲሰጡ በማለት ተለዋጭ ቀጠሮሰጥቶ ተነስቷል። መለስካቸው አምሃ ተጨማሪ ዝርዘር ልኳል።

33 ሰዎች የኦሮሞ ነፃነት ግንባርን ድርጅታዊ ህዋስ በመመሥረትና በአሸባሪነት ተከሰሱ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:19 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG