በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

"ከ10 ሺሕ ብር በላይ ይሸጡ የነበሩ ከብቶች ከ400 ብር ያነሰ እየተገመቱ ነው- የቦረና አርብቶ አደር


በኢትዮጵያ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ባገረሸው ድርቅ 5.7 ሚሊዮን ሕዝብ አስቸኳይ የምግብ ርዳታ ይፈልጋል። ድርቁ ባለፉት ዐስርት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ከታዩት የከፋ መሆኑ አሳሳቢ መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ገልፆ ሕዝቡን ከረሃብ ለመታደግ የሚያስችለውን ሥራ ለማከናወን 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ያስፈልጋል ብሏል።

በኢትዮጵያ በአምስት ክልሎች ከተከሰተው ድርቅ በተለይ በሁለቱ ክልሎች በኦሮሚያ እና በሶማሊያ የደረሰው ወደ አስከፊ ረሀብ ሊደርስ እንደሚችል ለጋሽ ድርጅቶች እያስጠነቀቁ ነው።
በአሁኑ ሰዓት ድርቁ ከብቶች እየጨረሰ ነው ከተባለበት አካባቢዎች አንዱ የሆነው የቦረና አርብቶ አደሮች ከብቶቻቸው እያለቁ መሆኑን ገልፀው የተረፉትን ገበያ ሲያወጧቸው ከ10 ሺሕ በላይ ይሸጡ የነበሩ ከብቶች ከ400 ብር ያነሰ እንደሚገመቱባቸው ይናገራሉ።
ጽዮን ግርማ ያጠናቀረችውን ዘገባ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

"ከ10 ሺሕ ብር በላይ ይሸጡ የነበሩ ከብቶች ከ400 ብር ያነሰ እየተገመቱ ነው- የቦረና አርብቶ አደር
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:56 0:00

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG