በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ሚሸል ኦባማ ከናይጀሪያ ሴቶች ጋር እንደሚቆሙ አስታወቁ


ልጆቻችንን መልሱ - ሚሼል ኦባማ /ዋይት ሃውስ/
ልጆቻችንን መልሱ - ሚሼል ኦባማ /ዋይት ሃውስ/

ደቡብ አፍሪካዊያን ለናይጀሪያዊያን ድጋፍ ወጥተዋል /ጆሃንስበርግ - ሐሙስ፤ ሚያዝያ 30/14/
ደቡብ አፍሪካዊያን ለናይጀሪያዊያን ድጋፍ ወጥተዋል /ጆሃንስበርግ - ሐሙስ፤ ሚያዝያ 30/14/
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:49 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

ናይጀሪያ ውስጥ ቦኮ ሃራም በሚባለው ፅንፈኛ ቡድን የተጠለፉ ወደ 300 የሚጠጉ ልጃገረዶችን ለመፈለግ ለሚደረገው ዓለምአቀፍ ጥረት ድጋፍ ለመስጠት የዩናይትድ ስቴትስ ቀዳሚት እመቤት ሚሼል ኦባማ ሃሽታግ ብሪንግ ባክ አወር ገርልስ (#BringBackOurGirls) - ልጆቻችንን መልሱ የሚል መልዕክት ይዘው የተነሱትን ፎቶግራፍ ትናንት በትዊተር ለቅቀዋል፡፡

የናይጀሪያ ሴቶች የሴቶች መብቶች ጉዳይ ነው ብለው በሚያምኑት በዚህ እንቅስቃሴ ውስጥ ሚስ ኦባማ ያደረጉትና ከጎናቸውም መቆማቸው ልባቸውን የነካው መሆኑን እየገለፁ ነው፡፡

አንዳንድ የፀጥታ ተንታኞች ደግሞ የዩናይትድ ስቴትስ በጉዳዩ ውስጥ መግባት ከሚኖረው ፋይዳ ይልቅ ጉዳቱ ሊያይል ይችላል የሚል ሥጋት እያሰሙ ነው፡፡

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
XS
SM
MD
LG