በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

-Fudade Mohammed- ውጤቱን በእርግጥም አደብዝዞታል። ሽብርተኝነቱን አወግዛለሁ።-Feke Burshea- መደብዘዙ ይደብዝዝ። ዋናው አነሱ ሰላም መሆናቸው ነው። ያሸነፈው ልጅ ለሞቱት ቤተሰቦች መፅናናትን በአሜሪካ ሚዲያ ቢመኝ ጥሩ ነው።-Haile Ayele-የሰው ልጅ ሙሉ በሙሉ በጥላቻ ሲሞላ እንዲህ ያለ ያለተገባ ድርጊት ይፈፅማል! ንፁህ ዜጋን እንደወጣ ማስቀረት እንስሳነት ነው!-Yihenew Wagachew-ውጤቱ እንዲያውም ያንፀባርቃል። የአሸባሪዎቹ አላማ ሰላምን ማደፍረስና ትኩረትን መሳብ ነው። ትልቅ መድረክ ስለሆነ። በዚህ ትልቅ መድረክ ማሸነፍ ደግሞ ድሉን አይረሴና አንፀባራቂ ያደርገዋል።-Teshi Tamrat-የማይረሳ ቀን ነው ለነሱ። ድል እና ሃዘን የተቀላቀለበት።-Abdurahman Ibrahim-በቦስተን ማራቶን የተደረገውን የሽብር ጥቃት አወግዛለሁ ግን በዚህ ብቻ አላቆምም! በኢራቅ የተገደሉትን፣ በበርማ፣ በፓለስታይን፣ በካሽሚር፣ በቦዝኒያ፣ በአፍጋኒስታን የሚደረጉትን ጅምላ ጭፍጨፋ በሙሉ አወግዛለሁ!-Sis Hiw-እንደው በሞቴ፥ አሁን ስለውጤት መደብዘዝ መነጋገሪያ ሰዓት ነው? እንኩዋን የጀግኖቻችን ህይወት አልደበዘዘብን፤ የተጎዱትንም ያረጋጋልን ካልን: በሁዋላ ይሄ በሄድንበት እየተከታተለ የንፁሃንን ህይወት የሚቀጥፈውን ፍንዳታ የመጨረሻ ድምፅ የምንሰማው መቼ ነው? ብንል ለስብእናችን የሚመጥን አይመስላችህም? ውድ ቪ.ኦ.ኤዎችም ይሄንን ርዕስ ብታነሱት ወይንም የመነጋግሪያ መንፈሱን ብትቀይሩት ሳይሻል ይቃራል ትላላችሁ?


Responses
XS
SM
MD
LG