በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኮንሶ ሰዎች አሁንም በጅምላ እንደሚታሰሩ፣ እንደሚደበደቡና ቀያቸውን ጥለው እየተሰደዱ እንደሆነ ተገለጸ


ፎቶ ፍይል፡ ኮንሶ ከተማ
ፎቶ ፍይል፡ ኮንሶ ከተማ

በኮንሶ ሰዎች አሁንም በጅምላ እንደሚታሰሩ፣የኮንሶን ሕዝብ ወክለው ጥያቄ ያቀርቡ የነበሩ የኮሚቴ አባላት የተወሰኑት መታሰራቸውን አብዛኞቹ ደግሞ መኖሪያ መንደራቸውን ትተው መሰደዳቸውን እኛም በስደት ጫካ ገብተን ነው የምናነጋግራችሁ ሲሉ ሁለት የኮንሶ ነዋሪዎች ነን ያሉ ለአሜሪካ ድምጽ ተናገሩ።

ያነጋገርናቸው ሁለት ሰዎች ቤተሰቦቻቸው እንደታሰሩባቸው፣ በኮንሶ የተነሳውን በዞን የመደራቸት ጥያቄ ያነሱ ሰዎች ቀያቸውን ጥለው ጫካ መግባታቸውንና እየተፈጠሩ ባሉት ሁኔታዎች ግራ እንደተጋቡ ለአሜሪካ ድምጽ ተናግረዋል።

የደቡብ ክልል መንግስት ቃል አቀባይ ወ/ሮ ሂክማ ኸይረዲን በተደጋጋሚ ስልክ ብንደውልላቸውም ስልካቸውን ሊያነሱልን ባለመቻላቸው ልናገኛቸው አልቻልንም።

በተመሳሳይ ለደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተደጋጋሚ የስልክ ሙከራ ብናደርግም ልናገኛቸው አልቻልንም።

ጽዮን ግርማ ዝርዝር አላት።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ድምጽ ያድምጡ።

በኮንሶ ሰዎች አሁንም በጅምላ እንደሚታሰሩ፣ እንደሚደበደቡና ቀያቸውን ጥለው እየተሰደዱ እንደሆነ ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:16:37 0:00

ተመሳሳይ ርእስ

XS
SM
MD
LG