በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

"ጨለማ ቤት ታስረናል"- የቂሊንጦ ማረሚያቤት ቃጠሎ ተከሳሾች


በነሐሴ ወር የቃጠሎ አደጋ የደረሰበት ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት
በነሐሴ ወር የቃጠሎ አደጋ የደረሰበት ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት

ቂሊንጦ ማረሚያ ቤትን በማቃጠል እና ለ23 ሰዎች ሞት ተጠያቂ ናችሁ በሚል የተከሰሱ 38 እስረኛ ተከሳሾች ጨለማ ቤት መታሰራቸውንና ከቤተሰብ መገናኘት እንዳልቻሉ በመግለፅ ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቀረቡ።

የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ እነ ማስረሻ ሰጤ ብሬ በሚል የክስ መዝገብ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ቃጠሎ በ23 ታራሚዎች ግድያና በሽብር ወንጀል ክስ የመሰረተባቸው የ38 እስረኛ ተጠርጣሪዎች ጉዳይ በዝግ ችሎት እንዲታይ ላቀረበው አቤቱና የተከሳቹ ጠበቆች መቃወሚያ አቀረቡ።

እስረኞቹ ጭለማ ቤት እንደታሰሩና በቤተሰብ መጎብኘት እንዳልቻሉ ለችሎቱ መናገራቸውን በዛሬው ዕለት በችሎት ላይ የተገኙ የአምስት ተከሳሾች ጠበቃ አቶ ሰኢድ አብደላ ለአሜሪካ ድምጽ ተናገሩ።

ጽዮን ግርማ ዝርዝር አላት።

ዝርዝርሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

"ጨለማ ቤት ታስረናል"- የቂሊንጦ ማረሚያቤት ቃጠሎ ተከሳሾች
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:39 0:00

XS
SM
MD
LG