በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት በኦሮሚያ ለተቀሰቀሰው ሁከት መንስዔ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ነው ብሏል


የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በላከው መግለጫ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ሰሞኑን በኦሮሚያ የተለያዩ ክፍሎችና የትምህርት ተቋማት ውስጥ ለተቀሰቀሰው ሁከት መንስዔ ነው ብሏል።

የከሠሩ የፖለቲካ ኃይሎችና በአሸባሪነት የተፈረጁ ድርጅቶች ያሠራጩት የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ሰሞኑን በኦሮሚያ የተለያዩ ክፍሎችና የትምህርት ተቋማት ውስጥ ለተቀሰቀሰው ሁከት መንስዔ ነው ሲል የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በላከው መግለጫ አስታውቋል።

ከጀርባ አሉ የተባሉትን ኃይሎች ማንነት መግለጫው በዝርዝር አልገለፀም፡፡ በተፈጠረው ሁከትም ሦስት ወጣቶች መገደላቸውን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሺነር ይፋ አድርገው ኅብረተሰቡን እያደናገሩ ናቸው ያሏቸውን አካላትም ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ አሳስበዋል።

መለስካቸው አምሃ ተጨማሪ ዝርዝር ልኳል ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያዳምጡ፡፡

የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት በኦሮሚያ ለተቀሰቀሰው ሁከት መንስዔ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ብሏል
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:56 0:00

XS
SM
MD
LG