በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኢትዮጵያ የኢንተርኔት ነፃነት የሌለባት ሀገር ተብላለች


መቀመጫውን በዋሽንግተን ዲሲ ያደረገው ፍሪደም ሃውስ የተባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት የ2016 የዓለማት የኢንተርኔት ነፃነት ደረጃን ይፋ ባደረገበት ሪፖርቱ ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሀገራት የኢንተርኔት ነጻነት በመገደብ አንደኛ ስትሆን ከ65 ሀገራት ደግሞ በአራተኛ ደረጃ ነፃነትን ገዳቢ ሀገር ተብላለች። ቻይና የኢንተርኔት ነጻነት በመገደብ 1ኛ ናት።

ፍሪደም ሀውስ Freedom on the Net 2016 (በኢንተርኔት ላይ ያለ ነፃነት) በሚል በትናንትናው ዕለት ባወጣው ሪፖርቱ በዓለም ላይ የኢንተርኔት አፈና እየጨመረ መምጣቱንና ጥናት ከተደረገባቸው 65 ሀገራት ውስት 35 በመቶ የሚሆኑት የኢንተርኔት ነፃነት የሌለባቸው መሆኑን ይፋ አድርጓል።

ፍሪደም ሀውስ ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የጎግል መስሪያ ቤት ሪፖርቱን ይፋ ሲያደርግ የተገኘችው ጽዮን ግርማ ተከታዩን ዘግባለች።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ድምፅ ያድምጡ

ኢትዮጵያ የኢንተርኔት ነፃነት የሌለባት ሀገር ተብላለች
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:52 0:00

XS
SM
MD
LG