በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አቶ ሀብታሙ አያሌው ወደ ውጭ ሄደው ለመታከም የሚያስችላቸው መረጃ መገኘቱ ተገለጸ


አቶ ሀብታሙ አያሌው
አቶ ሀብታሙ አያሌው

የቀድሞው የአንድነት ለፍትህና ዲሞክራሲ ፓርቲ አመራር አቶ ሀብታሙ አያሌው ወደ ውጭ አገር ሄደው ለመታከም የሚያስችላቸውን መረጃ መገኘቱን የቤተሰቡ የቅርብ ምንጮች ለአሜሪካ ድምፅ ገለጹ።

ህክምናው በዘገየ ቁጥር በሽታው ወደ ሌላ ደረጃ ሊያድግ እንደሚችል እና ለህክምናም እጅግ አስቸጋሪ እንደሚሆን ሃኪሞች መናገራቸውን የቤተሰቡ ምንጮች ተናግረዋል።

አቶ ሀብታሙ አያሌው የፈደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ቀደም ሲል ካቀረበው የሃኪም ማስረጃ በተጨማሪ የህክምና ቦርድ አባላት የፈረሙበት እና ታማሚው በግድ ወደ ውጭ ወጥቶ መታከም እንዳለበት የሚያረጋገጥ ማስረጃ እንዲያቀርብ በሰጠው ትእዛዝ መሰረት ይህን ማስረጃ ዛሬ ማግኘቱን የቅርብ ጓደኛው አቶ ዳኒኤል ስበሺ እና ቤተሰቡ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ።

አቶ ሀብታሙ አያሌው ወደ ውጭ ሄደው ለመታከም የሚያስችላቸው መረጃ መገኘቱ ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:35 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG