በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሳዑዲ ተመላሾች ቁጥር 37 ሺህ ደረሰ፤ በናሽቪል-ቴኔሲ ሰልፍ ተደረገ


የሳዑዲ ተመላሾች
የሳዑዲ ተመላሾች


please wait

No media source currently available

0:00 0:03:47 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

ሳዑዲ አረቢያ ከሚገኙ ኢትዮጵያዊያን እስካሁን 37 ሺህ የሚሆኑት አዲስ አበባ መግባታቸው ተገለፀ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን የጠቀሱ የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን እንዳሉት የተመላሾቱ ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ ነው።

በሌላ በኩል ደግሞ በይናዩትድ ስቴትስ ግዛቷ ቴኔሲ ዋና ከተማ ናሽቪል ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን ትናንት ሰኞ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገው ሳዑዲ አረቢያ በሚገኙ ወገኖቻቸው ላይ እየደረሰ ነው ያሉትን ኢሰብአዊ ድርጊት አውግዘዋል፡፡

ሻማ በማብራትም ወገኖቻቸውን በፀሎት አስበዋል፡፡

ስብሰባውን ካስተባበሩት ኢትዮጵያዊያን መካከል አቶ መርኃ ገብረእግዚአብሔር ለቪኦኤ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
XS
SM
MD
LG