ዋሺንግተን ዲሲ —
የፀረ አበረታች መድሃኒት ቢሮ ስፖርተኞች አበረታች ዕፅ መውሰድ አለመውሰዳቸውን መቆጣጠር መጀመሩንና ከ350 የሚበልጡ አትሌቶች ላይ ምርመራ ማድረጉን አስታውቋል።
ምርመራ ከተደረገባቸው የሚበዙት ሯጮች ሲሆኑ፤ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በበኩሉ፤ በአትሌቶች ዘንድ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ ጀምሯል።
የኢትዮጵያን የፀረ አበረታች መድኃኒት ሥራ አስመልክቶ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ውስጥ አበረታች መድሃኒቶችን ለማስቆም የሚንቀሳቀሰው ግብረ ኃይል አስተባባሪ ወ/ሮ ቅድስት ታደሰን ሔኖክ ሰማእግዜር አነጋግሯል።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ