በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ተቃዋሚዎቹ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር መነጋገር ይፈልጋሉ


አቶ አሥራት ጣሴ
አቶ አሥራት ጣሴ

ሰላሣ ሦስት የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በዚህ ዓመት የሚደረገው የአካባቢ ምርጫና ወደፊትም የሚካሄዱት ምርጫዎች እንደ 2002 ዓመተ ምኅረቱ ከሆኑ ለአገሪቱ ህልውናም አስጊ ናቸው አሉ።




please wait

No media source currently available

0:00 0:05:09 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

ፓርቲዎቹ ከዚህ አኳያ መንግሥት እንዲያነጋግራቸው ለጠቅላይ ሚኒስትር ፅሕፈት ቤት ጥያቄ እንደሚያቀርቡ አስታውቀዋል።

ባለፈው ወር አዳማ ከተማ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ2005 ዓ.ም የአባባቢ ምርጫን አስመልክቶ መርኃግብሩን ካሣወቀ በኋላ እነዚህ ፓርቲዎች ላቀረቡት የጋራ ጥያቄ “አጥጋቢ መልስ አልሰጠም” ሲሉ ሰላሣ ሦስቱ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ያቋቋሙት ጊዜያዊ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አሥራት ጣሴ ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡
አቶ አሥራት ጣሴ
አቶ አሥራት ጣሴ

በኢትዮጵያ የሚካሄዱት ምርጫዎች ነፃ፣ ፍትሐዊ፣ ሕጋዊና ተቀባይነት ያላቸው እንዲሆኑ ከተፈለገ ያለፈውን መንገድ መድገሙ ዋጋ የለውም፣ የበለጠ ችግርም ውስጥ ይከትተናል ብለዋል ፓርቲዎቹ፡፡

ይህ የፓርቲዎቹ ብቻ ዕምነት እንዳልሆነ የጠቆሙት አቶ አሥራት ጣሴ በ2002 ዓ.ም የተካሄደውን ሃገርአቀፍ ምርጫና ኢሕአዴግ 99.6 ከመቶ አሸንፌበታለሁ ያለበትን ምርጫ ዓለምአቀፍ ታዛቢዎች አይቀበሉትም” ብለዋል፡፡

ዝርዝሩን ከመለስካቸው አምኃ ዘገባ ያዳምጡ፡፡
XS
SM
MD
LG