አዲስ አበባ —
ዴሞክራሲ በሌለበትና ሰብዓዊ መብቶች ባልተከበሩበት ሁኔታ መልካም አስተዳደር ሊረጋገጥ አይችልም ሲሉ የመድረክ ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና ተናግረዋል፡፡
ኢሕአዴግ መልካም አስተዳደርን ስለማስፈን እያስቀመጠ ያለው ዕቅድም ከአንድ ሰሞን ግርግር አያልፍም ብለዋል፡፡
ገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ በተለይም ከአሥረኛው ድርጅታዊ ጉባዔው ጀምሮ በመልካም አስተዳደር ላይ አተኩሮ እንደሚሠራ እየገለፀ ይገኛል፡፡
እስክንድር ፍሬው ዘገባ አለው።
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡