በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ መንደሮች የምጣኔ ሀብት እድገት ፋይዳ


የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ መንደሮች የምጣኔ ሀብት እድገት ፋይዳ
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ መንደሮች የምጣኔ ሀብት እድገት ፋይዳ

የኢትዮጵያ መንግስት ለውጭ ገበያ የሚውሉ የኢንዱስትሪ ውጤቶችን የሚያመርቱ ጣቢዎች በስፋት በመገንባት ላይ ይገኛል። የሀገር ውስጥና በተለይ የውጭ ድርጅቶች በነዚህ የኢንዱስትሪ ጣቢያዎች ከጨርቃጨርቅ፣ እስከ ጫማና ሌሎች መገልገያዎችን እንዲያመርቱ በአንድ ስፍራ ለማሰባሰብ በማሰብ ነው በከፍተኛ መንግስታዊ ወጪ በመገንባት ላይ የሚገኙት።

በሐዋሳ ከተማ የተገነባው የኢንዱስትሪ መንደር ረቡእለት ተመርቆ ተከፍቷል።

ከ250 ሚሊዮን በላይ የአሜሪካ ዶላር እንደወጣበት የተገለጸው የሐዋሳ የኢንዱስትሪ ፓርክ በአጠቃላይ እስከ 60 ሺህ የሚጠጉ ስራዎችን እንደሚፈጥር ተገልጿል።

አጋሮቹም የዩናይትድ ስቴይትስ ኩባንያዎች መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ድዔታ አቶ ታደሰ ሃይሌ ለአሜሪካ ድምጽ ሬድዮ ገልጸዋል። ዝርዝሩን ከበታች የሚገኘውን የድምፅ ምልክት በመጫን ከቃለ-ምልልሱ ያድምጡ።

የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ መንደሮች የምጣኔ ሀብት እድገት ፋይዳ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:08 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG