የኢህአዴግ ማዕከላዊ ምክር ቤት በያዝነው ሳምንት መገባደጂያ በሚያካሂደው ስብሰባ በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩትን የፓርቲውን ሊቀመንበርና የአገሪቱን ጠቅላይ ሚንስትር አቶ መለስ ዜናዊን የሚተካ መሪ ይመርጣል ተብሎ ይጠበቃል።
በማእከላዊ ምክር ቤቱ ስብሰባና የምርጫ ሂደት፤ እንዲሁም ብዙዎችን ሲያነጋግር በሰነበተው በአገሪቱ ኅገ መንግስታዊ ድንጋጌ መሠረት አቶ መለስን በተጠባባቂ ጠቅላይ ሚንስትርነት የተኩት አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በመንግስት ብዙኃን መገናኛዎች በምክትል ጠቅላይ ሚንስርነት መጠራትና ሌሎች ተዛማች ርዕሶች ከውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዲሬክተር አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር የተካሄደ ቃለ ምልልስ ነው።