በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በኢህአዴግ ማዕከላዊ ምክር ቤት ስብሰባ የግንባሩና የአገሪቱ መሪዎች ይመርጣሉ።


በኢህአዴግ ማዕከላዊ ምክር ቤት የመሪዎች ምርጫ ሂደት፤ በወቅቱ የአገሪቱ መሪ ማንነትና ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የተካሄደ ቃለ ምልልስ።

በኢህአዴግ ማዕከላዊ ምክር ቤት ስብሰባ የግንባሩና የአገሪቱ መሪዎች ምርጫ
please wait

No media source currently available

0:00 0:12:57 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ


የኢህአዴግ ማዕከላዊ ምክር ቤት በያዝነው ሳምንት መገባደጂያ በሚያካሂደው ስብሰባ በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩትን የፓርቲውን ሊቀመንበርና የአገሪቱን ጠቅላይ ሚንስትር አቶ መለስ ዜናዊን የሚተካ መሪ ይመርጣል ተብሎ ይጠበቃል።

በማእከላዊ ምክር ቤቱ ስብሰባና የምርጫ ሂደት፤ እንዲሁም ብዙዎችን ሲያነጋግር በሰነበተው በአገሪቱ ኅገ መንግስታዊ ድንጋጌ መሠረት አቶ መለስን በተጠባባቂ ጠቅላይ ሚንስትርነት የተኩት አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በመንግስት ብዙኃን መገናኛዎች በምክትል ጠቅላይ ሚንስርነት መጠራትና ሌሎች ተዛማች ርዕሶች ከውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዲሬክተር አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር የተካሄደ ቃለ ምልልስ ነው።
XS
SM
MD
LG