በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የዲቪ ውጤት ተሠረዘ


ባለፈው ሣምንት ይፋ የተደረገው የዲቪ ዕድለኞች ዝርዝር መሠረዙን የአሜሪካ ኤምባሲ ኮንሱላር ባለሥልጣናት አስታወቁ፡፡

በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ ማክሰኞ ግንቦት 9 ቀን 2003 ዓ.ም ይፋ እንደተደረገው አአአ ለ2012 ዓ.ም ለዳይቨርሲቲ ቪዛ (ዲቪ ሎተሪ) አመልክተው ከነበሩ መካከል ዕድሉን አግኝታችኋል ተብለው ዝርዝራቸው ባለፈው ሣምንት በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ዌብ ሣይት ላይ የወጣው በሙሉ ተሠርዟል፡፡

ውጤቱ ውድቅ የተደረገው የዩናይትድ ስቴትስ ሕግ በሚያዘው መሠረት ማመልከቻዎቹ “በዘፈደ የመረጣ ዘዴ ስላልተስተናገዱ ነው” ተብሏል፡፡

ባለሥልጣናቱ ጨምረው እንዳስረዱት አመልካቾች አዲሱን ውጤት ከሐምሌ 8 ቀን 2003 ዓ.ም ጀምሮ እንዲጠብቁ አሳስበዋል፡፡

ተመሳሳይ ርእስ

XS
SM
MD
LG