በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በምዕራብ ዳላስ ቴክሳስ ድርቅ ለመቋቋምና ለማስወገድ የኢትዮጵያውያንን እንቅስቃሴ


በኢትዮጵያ የደረሰውን ድርቅ ለመቋቋምና ለማስወገድ፣ በምዕራብ ዳላስ ቴክሳስ የኢትዮጵያውያንን እንቅስቃሴ
በኢትዮጵያ የደረሰውን ድርቅ ለመቋቋምና ለማስወገድ፣ በምዕራብ ዳላስ ቴክሳስ የኢትዮጵያውያንን እንቅስቃሴ

በኢትዮጵያ የደረሰውን ድርቅ ለመቋቋምና ለማስወገድ፣ በድርቁም የሚጎዱ ወገኖችን ለመታደግ፣ ከአገር ውጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ-ኢትዮጵያ ዜጎች እርብርቦሽ እያደረጉ መሆናቸው ይታወቃል። ከዚህ አኳያ ዛሬ በምዕራብ ዳላስ ቴክሳስ የኢትዮጵያውያንን እንቅስቃሴ እንመለከታለን።

በኢትዮጵያ የደረሰውን ድርቅ ለመቋቋምና ለማስወገድ፣ በድርቁም የሚጎዱ ወገኖችን ለመታደግ፣ ከአገር ውጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ-ኢትዮጵያ ዜጎች እርብርቦሽ እያደረጉ መሆናቸው ይታወቃል።

ለዚህ ዓላማ የተቋቋመውን ግብረ-ኃይል ያሰባሰበው፣ በዳላስ የኢትዮጵያውያን መረዳጃ ማኅበር ነው። ስለ መጪው እሑድ እ.አ.አ. ኤፕሪል 3 ቀን 2016 የገንዘብ አሰባሰብ ዝግጅትና መርሓ-ግብር አስተያየታችውን ለቪኦኤ የሰጡት ደግሞ፣ የመረዳጃ ማኅበሩ ዳይሬክረተር አቶ ብርሃን መኰንን እና የግብረ-ኋይሉ ቡድን የሕዝብ ግንኙነት ኋላፊ ወይዘሪት የትናየት ሳሙኤል ናቸው።

በምዕራብ ዳላስ ቴክሳስ ድርቅ ለመቋቋምና ለማስወገድ የኢትዮጵያውያንን እንቅስቃሴ
በምዕራብ ዳላስ ቴክሳስ ድርቅ ለመቋቋምና ለማስወገድ የኢትዮጵያውያንን እንቅስቃሴ

አቶ ብርሃን በሰጡት አስተያየት፣ ቢያንስ እስከ 200 ሰው እንደሚጠብቁና በትንሹ አንድ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር ለማሰባሰብ እንዳቀዱ ተናግረዋል።

የግብረ-ኃይሉ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዋ ወ/ት የትናየት በበሉላቸው፣ አብያተ-ክርስቲያናት፣ መስጂዶችና ሌሎችም ሕዝባዊ ተቋማት ለዚህ ዓላማ ታጥቀው እንደተነሱ፣ ይልቁንም ወጣቱ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሆነ አመልክተዋል።

ዝርዝሩን ለማዳመጥ ከዚህ በታች ያለውን ፋይል በመጫን ያድምጡ።

በምዕራብ ዳላስ ቴክሳስ ድርቅ ለመቋቋምና ለማስወገድ የኢትዮጵያውያንን እንቅስቃሴ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:55 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

XS
SM
MD
LG