በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሴንትር አፍሪኳ ባንጋሱ ሁኔታው ጨርሶ እየተበላሸ ነው


ፎቶ ፋይል
ፎቶ ፋይል

በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ባንጋሱ ከተማ ሰላሣ ሲቪሎችና ስድስት ሰላም አስከባሪ ወታደሮች በአማፂያን ተገደሉ፡፡

በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ባንጋሱ ከተማ ሰላሣ ሲቪሎችና ስድስት ሰላም አስከባሪ ወታደሮች በአማፂያን ተገደሉ፡፡

ከማዕከል ርቃ በምትገኘው ከተማ ውስጥ አማፂያኑ እያካሄዱ ባሉት ዘመቻ ሙስሊሞች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እየፈፀሙ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

ባንጋሱ ውስጥ በተከፈተባቸው ጥቃት ምክንያት እየተፈናቀሉ ያሉት ሲቪሎች በአንድ መስጂድ፣ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስትያን እና በድንበር የለሽ ሃኪሞች ሆስፒታል ውስጥ ጥገኝነት እግኝተው መጠለላቸውን ሚኑስካ በሚል ምኅፃር የሚታወቀው በሴንትር አፍሪክ የተባበሩት መንግሥታት ዘርፈ ብዙ የተቀናጀ ማረጋጋት ተልዕኮ አስታውቋል፡፡

የመንግሥታቱ ድርጅት ኃይሎች ባንጋሱን ፈጥነው ለመቆጣጠር እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውን ለሮይተርስ የተናገሩት የማኑስካ አዛዥ ፓርፌ ኦናንጋ ኦኛንጋ በአካባቢው ያለውን ሁኔታ «እጅግ የተበላሸ» ሲሉ ገልፀውታል፡፡

ተገድደው ብረት እንዲጨብጡ የተደረጉ ሕፃናት ወታደሮችም ከጥቃት አድራሾቹ መካከል እንደሚገኙ ኦኛንጋ አክለው ጠቁመዋል፡፡

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG