በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ከፍተኛው የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፑብሊክ ፍርድ ቤት፣ ባለፈው ወር የተካሄደውን የምክር ቤት ምርጫ ሰርዘ


ከፍተኛው የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፑብሊክ ፍርድ ቤት ባለፈው ወር የተካሄደውን የምክር ቤት ምርጫ ሰርዟል። ሁለት የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትሮች ግን ለፕረዚዳንትነት የማጣርያ ምርጫ እንደሚወዳደሩ አረጋግጧል።

የሀገሪቱ ህገ-መንግስታዊ ፍርድ ቤት እአአ ባለፈው ታህዝሳስ 30 ቀን የተከሄደው የመጀመርያ ዙር የምክር ቤት ምርጫ ብዙ ጉድለቶች እንደነበሩበት ገልጿል። አንዳንድ ተወዳዳሪዎች በጉዳዩ የተሳተፉ ይመስላል ሲል አክሎበታል።

በምርጫው ስለታዩ ጉድለቶች የሚገልጹ ከአራት መቶ በላይ ስሞታዎች ለምርጭ ባለስልጣኖች እንደቀርቡ የፍርድ ቤቱ ፕረዚዳንት ዛካሪ ንዱምባ (Zacharie Ndoumba) ገልጸዋል።

ኤንሰት ጆርጅስ ዶጉሌ (Anicet Georges Dologuele) እና ፋውስቲን አርቻንገ ቷደራ (Faustin Archange Touadera) የተባሉት በመጀመርያው ፕረዚዳንታዊ ምርጫ ከፍተኛ ድምጽ ያገኙት ተወዳዳሪዎች ግን የማጣርያ ምርጫ እንደሚያካሄዱ ከፍተኛው ፍርድ ቤት አረጋጋጧል። በመጀመርያው ምርጫ ውጤት መሰረት ዶጉሌ (Dologuele) 24 ከመቶ ቷደራ (Touadera) ደግሞ 19 ከመቶ ድምጽ አግኝተዋል።

XS
SM
MD
LG