በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ሞቃዲሾ የተጠመደ ቦምብ ፈንድቶ አምስት ሰዎችን ገደለ


ሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ የደረሰው ፍንዳታ
ሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ የደረሰው ፍንዳታ

ሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ ውስጥ ዛሬ ረቡዕ መኪና ላይ የተጠመደ ቦምብ ፈንድቶ አምስት የፀጥታ ጥበቃ አባላት እና አንድ የተቀባረ ፈንጂዎች ኤክስፕርት ገደለ።

ሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ ውስጥ ዛሬ ረቡዕ መኪና ላይ የተጠመደ ቦምብ ፈንድቶ አምስት የፀጥታ ጥበቃ አባላት እና አንድ የተቀባረ ፈንጂዎች ኤክስፕርት ገደለ።

የሶማሊያ ፖሊስ ቃል አቀባይ ማሐመድ ዩሱፍ ኦማር ማዳሌ ሲናገሩ ቦምብ የተጠመደባት መኪና ሞቃዲሾ ዋዳጂር ቀበሌ ፖሊስ ጣቢያ አጠገብ ቆማ እንደነበረ እና የፀጥታ ኃይሎች ተጠራጥረው የመኪናዋን አሽከርካሪ አስረው ፈንጂውን ለማምከን ሲሞክሩ እንደፈንዳባቸው ገልፀዋል።

ለጥቃቱ እስካሁን ኃላፊነት የወሰደ ወገን የለም። ይሁን እንጂ እንዲህ ያሉ ሽብርተኛ ጥቃቶችን በማድረስ ብዙውን ጊዜ የሚጠረጠረው ፅንፈኛው ቡድን አልሸባብ ነው።

የፌስቡክ አስተያየት መስጫ

XS
SM
MD
LG