በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አባላት በቡለን ወረዳ ታስረው መለቀቃቸውን አስታወቁ


አቶ ይልቃል ጌትነት - የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር
አቶ ይልቃል ጌትነት - የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር

የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ውስጥ የተፈናቀሉ አርሶ አደሮች የሚገኙበት ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑን የተለያዩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መግለፃቸውን ቀጥለዋል፡፡




ቤንሻንጉል-ጉምዝ
ቤንሻንጉል-ጉምዝ

please wait

No media source currently available

0:00 0:06:08 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

የቤንሻንጉል-ጉምዝ ወረዳዎች
የቤንሻንጉል-ጉምዝ ወረዳዎች
የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ውስጥ የተፈናቀሉ አርሶ አደሮች የሚገኙበት ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑን የተለያዩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መግለፃቸውን ቀጥለዋል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ
ሰማያዊ ፓርቲ

ወደ ቡለን ወረዳ በመጓዝ በአካባቢው ያለውን ሁኔታ ተመልክተው መመለሣቸውን የተናገሩት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ይልቃል ጌትነት “ችግሩ አሁንም አልተቀረፈም” ብለዋል፡፡

የወረዳው አስተዳዳሪ ግን “ስለአርሦ አደሮቹ እየተሠራጩ ያሉት ወሬዎች የተሣሣቱ ናቸው” ይላሉ፡፡ ፌደራሉ መንግሥት በጉዳዩ ላይ የሰጠው አስተያየት የለም፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በሰጡት መግለጫ ደግሞ “ሁኔታው የወረዳው አስተዳዳሪ ከሰጡት መግለጫ የተለየ ነው” ብለዋል፡፡
አቶ ይልቃል ጌትነት - የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር
አቶ ይልቃል ጌትነት - የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር

እርሣቸውና ሌሎችም የፓርቲያቸው አመራር አባላት ለአምስት ሰዓታት በወረዳው ፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው እንደነበረና በምሥል የያዟቸው ማስረጃዎች በፖሊስ አባላቱ እንደተሠረዙባቸው አመልክተዋል፡፡

ዝርዝሩን ከእስክንድር ፍሬው ዘገባ ያዳምጡ፡፡
XS
SM
MD
LG