በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በባንግላዴሽ እሥልምና ፓርቲ መሪ ላይ የተላለፈው የሞት ፍርድ ፀና


የባንግላዴሽ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ይደግፋሉ፤/AP Photo)
የባንግላዴሽ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ይደግፋሉ፤/AP Photo)

የባንግላዴሽ እሥልምና ፓርቲ መሪ ሃገሪቱ ከፓኪስታን ጋር እአአ በ1971 ዓ.ም ባካሄደችው የነፃነት ውጊያ ወቅት የነበራቸውን ሥልጣን መከታ በማድረግ ፈፅመዋቸዋል በተባሉ ወንጀሎች የተከሰሱት ባለፈው ዓመት ጥቅምት ውስጥ ነበር፡፡

ባንግላዴሽ ውስጥ የሚገኘው ትልቁ የእሥልምና ፓርቲ መሪ በጦር ወንጀለኛነት የተላለፈባቸውን የሞት ፍርድ፣ የሃገሪቱ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዛሬ ረቡዕ እንዳፀናው ተገለጸ።

አክራሪውን ጃማአት ኤ ኢስላሚ ፓርቲ ይመሩ የነበሩት የቀድሞ ካቢኔ አባል የነበሩት ሞቲዉር ራህማን ኒዛሚ ያቀረቡት ይግባኝ ውድቅ የተደረገው በአንድ የፍርዱ ሸንጎ ላይ በተሰየሙ የዳኞች ቡድን መሆኑም ታውቋል።

ኒዛሚ ባንግላዴሽ ከፓኪስታን ጋር እአአ በ1971 ባካሄደችው የነፃነት ውጊያ ወቅት የነበራቸውን ሥልጣን መከታ በማድለግ እንደፈፀሟቸው በተነገረ ጅምላ ግድያ፣ ወከባ፣ መድፈርና ንብረት ማውደም ወንጀሎች የተከሰሱት ባለፈው ዓመት ጥቅምት ውስጥ ነበር።

ለዘገባው የተያያዘውን የድምጽ ፋይል ያዳምጡ።

የባንግላዴሽ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የእምስልምና ፓርቲ መሪውን በጦር ወንጀለኛነት የሞት ፍርድ እንዳጸናው ተገለጸ
please wait

No media source currently available

0:00 0:01:00 0:00

XS
SM
MD
LG