በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አረና ቅስቀሣውን አቋረጠ፤ በአባሎቹ ላይ ጥቃት መፈፀሙን አስታወቀ


አቶ ሄድሮም ኃይለሥላሴ
አቶ ሄድሮም ኃይለሥላሴ

ተቃዋሚው አረና ትግራይ “በአባሎቼ ላይ ተፈፅሟል” ባለው ድብደባና ለምርጫ ቅስቀሣ ሥራ በተከራያት መለስተኛ አውቶቡስ ላይ በደረሰው ጉዳት ምክንያት በመላው የትግራይ ክልል የጀመረውን የምረጡኝ ቅስቀሣ ዛሬ ማቋረጡን ይፋ አድርጓል።

አረና ቅስቀሣ ሲያካሂድባት የነበረች፣ ጉዳት የደረሰባት ሚኒባስ
አረና ቅስቀሣ ሲያካሂድባት የነበረች፣ ጉዳት የደረሰባት ሚኒባስ

please wait

No media source currently available

0:00 0:07:44 0:00
ቀጥተኛ መገናኛ

ተቃዋሚው አረና ትግራይ “በአባሎቼ ላይ ተፈፅሟል” ባለው ድብደባና ለምርጫ ቅስቀሣ ሥራ በተከራያት መለስተኛ አውቶቡስ ላይ በደረሰው ጉዳት ምክንያት በመላው የትግራይ ክልል የጀመረውን የምረጡኝ ቅስቀሣ ዛሬ ማቋረጡን ይፋ አድርጓል።

ዘጋቢያችን ግርማይ ገብሩ የተሽከርካሪዋ የኋላ መስትዋትና መብራት መሰባበሩን በሥፍራው በአካል ተገኝቶ ተመልክቷል።

ድብደባ ተፈፀመብን ከሚሉ ሰዎች መካከል ደግሞ ከአፅቢ ከተማ የመጡት አቶ ሄድሮም ኃይለሥላሴ እራሣቸው ላይ በመፈንከታቸው መቀሌ ውስጥ ሕክምና ማግኘታቸው ተገልጿል፡፡

አረና “የህወሓት ካድሬዎች ያደራጇቸው ወጣቶች አድርሰውታል” ያለውን ጥቃት አስመልክቶ የክልሉ የፀጥታና የአስተዳደር ኃላፊ አቶ ሓዱሽ ዘነበ ተጠይቀው “ተፈጽሟል የተባለውን ጥቃት ለማጣራት መርማሪዎቻችንን ወደ አካባቢው ልከናል፤” ብለዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

XS
SM
MD
LG